Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, August 31, 2015

በቡሌሆራ ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎቸ ተጎዱ

በቡሌሆራ ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎቸ ተጎዱ
ነኅሴ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነሃሴ 19 ቀን በኦሮምያ ክልል በቡሌሆራ ከተማ፣ በ1949 የተገነባውን የገበያ ማእከል በማፍረስ የመኪና መናሃሪያ ለማድረግ፣ እንቅስቃሴ በተጀመረበት ወቅት ህዝቡ ያሰማውን ተቃውሞ ተከትሎ ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ ከ150 በላይ ሰዎች በድብደባ ሲቆስሉ፣ ወገኖ ወንዳቸው የተባለ ወጣት በጥይት ተመትቶ ሆስፒታል ገብቶ እየታከመ ነው። የከተማው ባለስልጣናት ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ሳይስማሙና ለነጋዴዎቹ አስፈላጊውን ካሳ ሳይከፍሉ የማፍረሻ መኪኖችን በመያዝ ማፍረስ መጀመራቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ ህዝቡ ድርጊቱን እንዳየ በባለስልጣኖቹ ላይ ድንጋይ በመወርወር ተቃውሞውን ገልጿል። ፖሊሶች ተኩስ በመክፈት ህዝቡን ለመበተን ሙከራ ቢያደርጉም፣ ግጭቱ ለሰአታት ቆይቷል። በፖሊስ ዱላና ጥይት የቆሰሉት በአንቡላንስ እየተጫኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል። ይህንን ተከትሎ ፖሊሶች እስከ ሌሊት ድረስ ወደ መኖሪያ ቤቶች እየገቡ ነፍሰጡሮችን ሳይቀር ደብድበዋል። በእለቱ 26 ሰዎች ሲታሰሩ፣ 13 ተለቀው፣ 13 ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። አቶ ታደለ ቢቂላ የተባሉ አባት ልጃቸው ታደለ ቢቂላ ክፉኛ መደብደቡን ተከትሎ ወደ ሆስፒታል ሲሄዱ፣ ልጄን ፖሊስ ደብድቦብኝ ነው ብለው በመናገራቸው የተባሱጩት ፖሊሶች እርሳቸውንም ከ13ቱ ተከሳሾች መካከል በመቀላቀል ፍርድ ቤት አቅርበዋቸዋል። የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ ጌታቸው በቀለ፣ ፖሊስ የወሰደውን እርምጃ አውግዘዋል። ለተጎዱት ቤተሰቦች አስቸኳይ ካሳ እንዲከፈላቸው አቶ ጌታቸው ጠይቀዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ከምርጫው በሁዋላ ከ2 ሺ ያላነሱ የኦሮሞ ተወላጆች መታሰራቸውን የምስራቅ አፍሪካ የሰብአዊ መብት ሊግ ገልጿል። ሊጉ ባወጣው መግለጫ በቡሌ ሆራ፣ ደምቢ ዶሎ፣ ምእራብና ሰሜን ሸዋ ዞን አፈሳው ተጧጡፏል። በዋራ ጃርሶ ወረዳ ከ400 በላይ አርሶአደሮች አመጽያንን አስጠግታችሁዋል በሚል መታሰራቸውን አስታውቓል። ከታሰሩት መካካል የ20 ሰዎችን ስም ይፋ አድርጓል።

የሱዳን ወታደሮች 8 ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደሉ



የሱዳን ወታደሮች ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደሉ
ነኅሴ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሱዳን ባለሀብቶች መተማ ዮሃንስ ከተማ ውስጥ "ትራክተር መንዳት የሚችል 11 ሰዎችን እንፈልጋለን" የሚል ማስታወቂያ መለጠፋቸውን ተከትሎ፣ ውድድሩን ካለፉት መካካል 8ቱ በሱዳን ታጣቂዎች ታርደው ተገድለዋል። ባለሀብቶቹ በርካታ አመልካቾችን ቢያገኙም፣ አስራ አንዱን ብቻ ይዘው ወደ ሱዳን መሄዳቸውን ፣ ይሁን እንጅ ሱዳን ውስጥ ሲገቡ፣ ወታደሮቹ መንገድ ላይ ጠብቀው ከመኪና ላይ በመውጣት ሰዎችን ማረድ ሲጀምሩ፣ የውትድርና ትምህርት የነበራቸው 3 ወጣቶች ከመኪና ላይ በመውረድ ማምለጣቸውን፣ ቀሪዎቹ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። የተወሰኑ አስከሬዎች መቃጠላቸውን፣ የተወሰኑት ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ኢሳት የወረዳውን አስተዳዳሪ ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም ሊሳካለት አልቻለም። ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ድንበር እንዲካለል ሰሞኑን በድጋሜ ጠይቃለች። ከዚህ ቀደም እጅግ ሰፊ የሆነ መሬት ከኢትዮጵያ የወሰደችው ሱዳን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ያሉ አወዛጋቢ ቦታዎች እንዲካለሉላት ትፈልጋለች። በኢትዮጵያውያን ላይ የተወሰደውን እርምጃ በተመለከተ የኢህአዴግ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እስካሁን ምንም አላለም።

አሰቃቂው ግድያ
----
1ታደለ አበጀ
2 ቴዴ ሸመዴ
3 የሁንሰ አሰናቀው
4 ታከለ አህመድ
5 እሸቱ ዳውድ
6 ባህሩ ቃኝው
7 ሀሰን
8 ታዮ ሙላለም የተባሉ ወጣቶች አካባቢው ይገባናል በሚሉ የሱዳን
ታጣቂዎች ስለ መገደላቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ። በረከት በተባለው አካባቢ
አሰቃቂ ግድያ የተፈጸመባቸው ወጣቶች አስከሬን በምስሉ የሚታየው
ነው።የሱዳኑ ትሪቡን ጋዜጣ ባሳለፍነው ሳምንት ሱዳን የድንበር ማካለሉ
ኦፊሻሊ እንዲከናወን መጠየቁ አይዘነጋም።
.

Netsanet Beqalu Mannet's photo.

Netsanet Beqalu Mannet's photo.

ሱዳን የ250ካሬ ኪ.ሜ የቆዳስፋት መሬት እንደገና ይካለል ዘንድ ለኢትዮጵያ መንግስት ጥሪ አደረገች (አዋዜ)

ሱዳን ከአማራ ክልል ጋር በምትዋሰንበት በኩል የሚገኘውንና ሶስት ወንዞች የሚያቋርጡትን የ250ካሬ ኪ.ሜ የቆዳስፋት መሬት እንደገና ይካለል ዘንድ ለኢትዮጵያ መንግስት ጥሪ አደረገች (አዋዜ)
መንግስት ጥሪ አደረገች (አዋዜ)
August 30th, 2015

የሱዳን ገዳሪፍ ግዛት ሀገረ ገዢ ሜርጋኔ ሳሌህ በኢትዮጵያና በሰዳን መካከል አለ ብለው የሚያምኑት የረጅም ግዜ የድንበር ውዝግብ ይፈታ ዘንድ ድንበሩ እንዲካለል መጠየቃቸው ተሰማ፡፡ ሄራል ትርቢውን የተሰኘው ጋዜጣ ትላንት እንደዘገበው ሱዳን በምስራቃዊ ግዛቴ ገዳሪፍ ደቡብ ምስራቅ አል-ፍልሻጋ በተባለው አከባቢ ይገኛል የምትለውና የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬታችው መሆኑን ሚናገሩለትን ይህን ምሬት ጉዳይ ከቀ/ጠ/ሚ/ አቶ/መለሰ ዜናዊ ግዜ ተጀምሮ እሳቸው ድንገት በመሞታቸው መቋረጡን ያስታውሳል ጋዜጣው፡፡ 

Three Ethiopian athlets stood 1-2-3 in 5000 meter race in Bejing




በቤጂንግ፣ ቻይና የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በተጠናቀቀው አስደናቂ የሴቶች 5000ሜ አልማዝ አያና፣ ሲንቢሬ ተፈሪ እና ገንዘቤ ዲባባ ተከታትለው በመግባት ታሪክ ሰርተዋል።





Beijing: Almaz Ayana led an Ethiopian medals sweep in the women’s 5,000m on Sunday as 1,500m winner Genzebe Dibaba had to settle for bronze at the world championships in Beijing.
In cool conditions after heavy rain, Ayana ran a championships record 14min 26.83sec to win comfortably from Senbere Teferi, who put on a late surge to pip Dibaba by seven-hundredths.
Dibaba, younger sister of 5,000m world record-holder Tirunesh, had already won the 1,500m, but Ayana’s pace over the last five laps put paid to her hopes of a double.
“I had to win the gold medal!” said Ayana. “It was a hard race and a hard competition in general. It is great for our country that we won gold, silver and bronze.”
Dibaba said she was “not disappointed” with bronze and added that she had been hampered by a heel injury since winning her maiden world championships gold in the 1,500m.
“My country won three medals, I can only be pleased about that,” Dibaba said.
“It was a really hard race. I’ve had so many races recently and after the 1,500m final, my left foot started to pain me — I have a heel spur that hurts a lot.
“This race was so tough for me because of this injury. My shape (fitness) was at its best.”
Dibaba, whose world record in the 1,500m in Lausanne last month was the fourth she currently holds, looked comfortable for the first half of the race.
Japanese pair Misaki Onishi and Ayuko Suzuki raced out to an early lead, tracked by Dibaba in the 12-and-a-half lap event.
The chase group comprised the Ethiopians Dibaba, Ayana and Teferi, Kenyan quartet Viola Kibiwot, Mercy Cherono, Irene Cheptai and Janet Kisa, and Ethiopian-born Bahraini Mimi Belete.
With seven laps to go, the Japanese were dropped and an Ayana surge, tracked by Dibaba and Cherono, strung out the 15-woman field.
Some 800 metres later and the Ethiopian duo were out by themselves.
Ayana, who was only competing in the 5,000m, kicked again and built up a 50-metre lead on Dibaba, her eyes glued to the big screen as she monitored her pursuer’s position.
Ayana hit the bell for the last lap even further ahead and she maintained her advantage for a comprehensive victory.
Dibaba’s woes were compounded when a fast-finishing Teferi caught her at the line to take silver in 14:44.07.
“The tactics were not prepared but three Ethiopian girls on the podium is very important for our federation and athletics in our country,” said Teferi.
Source: NDTV Sport
Image result for the ethiopian women 5000 meter athletes in beijing

Sunday, August 30, 2015

ዝዋይ ላይ ከፍተኛ የመኪና አደጋ ደረሰ * ነዳጅ የያዘው መኪና ቃጠሎ አስከትሎ ሁለት ሰዎች ተቃጥለው ሞቱ


ዝዋይ ላይ ከፍተኛ የመኪና አደጋ ደረሰ * ነዳጅ የያዘው መኪና ቃጠሎ አስከትሎ ሁለት ሰዎች ተቃጥለው ሞቱ








(ዘ-ሐበሻ) በኢትዮጵያ ከ እለት ወደ እለት እየደረሰ ያለው የመኪና አደጋ አስፈሪና በተለይም በመኪና ረዥም መንገድ መሄድን የማያስመኝ እየሆነ መጥቷል:: ዛሬ ጠዋት ላይ በዝዋይ ከተማ አካባቢ በደረሰ የመኪና አደጋ ወደ እሳትነት ተቀይሯል::

ከአካባቢው ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ነዳጅ የያዘው የጭነት መኪና ከሕዝብ ንብረት ማመላለሻ አይሱዙ መኪና ጋር የተጋጩ ሲሆን ነዳጅ የያዘው መኪና እሳት ተነስቶበት ለሁለቱም መኪኖች መቃጠል ምክንያት ሆኗል:: እስካሁን የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት የመኪናዎቹ አስከርካሪዎች የሁኑ 2 ሰዎች ተቃጥለው ሕይወታቸው አልፏል:: ሆኖም ግን ፖሊስ ሰፋ ያለ ማብራሪያ የሰጠው ነገር የለም::

source: Zehabesha

Mare Dibaba Wins the First Women’s Marathon for Ethiopia at World Championships



BEIJING (AP) — Mare Dibaba captured the first women’s marathon title for Ethiopia at the world championships Sunday, holding off Helah Kiprop of Kenya in a race that was settled by a 100-meter sprint.
Dibaba finished in 2 hours, 27 minutes, 35 seconds, but needed to pick up the pace after entering the Bird’s Nest to hold off Kiprop, who finished one second behind in the closest finish ever at the worlds. Eunice Kirwa of Bahrain earned the bronze.
Two-time champion Edna Kiplagat was in contention until the end but faded to fifth place.
With the stadium in sight, Dibaba kept checking her watch, waiting to make her move. Just after entering the tunnel, she took control and raised her arms after crossing the line.
She certainly has a fitting name for a champion. However, she’s not related to Ethiopian long-distance greats Tirunesh and Genzebe Dibaba.
Around the two-hour mark, Kiplagat said something to her two Kenyan teammates and they began to pick up the pace. A pack of a dozen runners was thinned to six.
That group included the Kenyans, Dibaba and Kirwa, who is Kenyan and started to compete for Bahrain in 2013. Soon after, Kiplagat dropped back, too.
It was an overcast day that was missing the baking heat the men encountered on the opening day of the championships. The air quality wasn’t ideal, though, with the race starting at the “moderate” level and staying in the “unhealthy for sensitive groups” range until the finish.
Image result for mare dibaba beijing

አቶ በረከት ስምኦን በማሌዢያ ፒናንግ ደሴት የንግድ እና መኖሪያ ሕንጻ ቤት እያስገነቡ ነው::





አቶ በረከት ስምኦን በማሌዢያ ፒናንግ ደሴት የንግድ እና መኖሪያ ሕንጻ ቤት እያስገነቡ ነው::
‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Corruption‬ ‪#‎EthiopianOppositionParties‬ ‪#‎EPRDF‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬

Minilik Salsawi - የለውጥ ሃይሉ እርስ በእርሱ በፖለቲካ ጥላቻ ሲጠዛጠዝ በሃገር እና ሕዝብ ላይ ዘረፋው ቀጥሏል:-ከጸረ - ሙስና ኮሚሽን ከመዝገብ ቁጥር /203/2007 ከተገኘው መረጃ መሰረት አቶ በረከት ስምኦን በማሌዥያ ፒናንግ ደሴት ጃላን ባሩው 62 በተባለ ቦታ ላይ በሚሊዮኖች ዶላር በወጣ ወጪ ኢትዮጵያ ውስጥ በብረታብረት ስራዎች ላይ ከሚገንኝ አንድ ማሌዢያዊ ጋር በመቀናጀት እጅግ ዘመናዊ የንግድ እና መኖሪያ ሕንጻ በኢንቨስትመት ስም እያስገነቡ መሆኑን ጥቆማ ለኮሚሽኑ ደርሶ በመመዝገብ እያጣራ መሆኑ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል::ከሼህ መሃመድ አላሙዲ የሃገሪቱን ሃብት እያሳለፉ እየሰጡ ከፍተኛ ገንዘብ የሚረከቡት ኤርትራዊው አቶ በረከት ስምኦን በግልጽ ከሚታወቀው ከአገር ቤቱ በካፒቴኑ ስም ካስመዘገቡት ሆቴል እና ማደያዎች እንዲሁም የሪያል ስቴቶች በተጨማሪ በዱባይ እና አቡዳቢ መኖሪያቤቶች እና አክሲዮኖች ሲኖሯቸው እንዲሁም በሚላን ጣሊያን መኖሪያ ቤት በሕንድ የሚስማር ፋብሪካ ባለድርሻ ናቸው የሚል ከዚህ ቀደም በጸረ ሙስና ኮሚሽን የተመዘገበ ፋይል አላቸው::


የጸረ ሙስና ኮሚሽን በሕወሓት ባለስልጣናት በተለይ በአቶ ደብረጽዮን እና በጄኔራል? ሳሞራ ልዩ ትእዛዝ የሚመራ ሲሆን በከፍተኛ ባለስልጣናት ላይ የሚመጡ መዝገቦች ከቦታቸው እንዳይንቅሳቀሱ እና ተጣርተው ማረጋገጫ እንደተገኘ ከነማስረጃቸው ታሽገው ቀጥታ ወደ ደህንነት ቢሮ እደሚላኩ ይታወቃል::የአቶ በረከት የመኖሪያ ቤት ግንባታም ጠቅላላ መዝገቡ እንዳለቀ በጥብቅ ምስጢር በሚል ለደህንነት ቢሮ እንደሚላክ ምጮቹ የጠቆሙ ሲሆን የከፍተኛ ባለስልጣናትን ጉዳይ በሚመረምሩ መርማሪያን ላይ ክፍተኛ የሆነ የደህንነት ክትትል እንደሚደረግ ምንጮቹ አክለው ጠቁምዋል::

የደህንነት ቢሮው በቅርቡ ያወጣቸው መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ባለስልጣኖች በተለያዩ ሃገራት የሰሯቸው መኖሪያ ሕንጻዎች መታገዳቸው ይታወቃል::የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣናት ኬንያ እና ሱዳንን ጨምሮ በተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት መኖሪያ ቤቶች የሰሩ ሲሆን በታንጋኒካ ውስጥ ሃይቅ ዳርቻ ላይ የግል የመዝናኛ ቦታ ለመገንባት ያመለከቱ የሕወሓት ባለስልጣናት ከታንጋኒካ ባለስልጣናት ጋር በቦታ መረጣ እና በጉቦ ገንዘብ አለመግባባት እስካሁን እንዳልተፈቀደላቸው ታውቋል:: ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

ከዊሃ እስከ ኦምሃጀር – አንድ ሰሞን ከአርበኞች ጋር (ኤፍሬም ማዴቦ)

በኤፍሬም ማዴቦ
ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ። አዎ! ማተቡን ላጠበቀና በአምላኩ ለሚታመን በእርግጥ ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ። ሰዉ ነኝና እንደ ፈጣሪ ቃሌ ሁሉ እዉነት ነዉ ብዬ አለተፈጥሮዬ አላብጥም። ግን ሰዉ ብሆንም ፈጣሪዬን የምፈራ ሰዉ ነኝና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ስል ልቦናዬ እያወቀዉ እንደነ ጋሼ እንደልቡ ዉሸት ደርድሬ ለአንባቢ የማቀርብበት ምንም ምክንያት የለም። ከዚህ ቀጥሎ የማስነብባችሁ እያንዳንዱ ቃል እንደ ዳያስፖራ ተረተኞች የምተርተዉ ‘ሰዉ ሰዉ’ የማይሸተት ተረት ሳይሆን ኢትዮጵያ ድንበር ላይ በየግንባሩ የተሰለፉትንና በስልጠና ላይ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አርበኞች ስጎበኝ በአይኔ ያየሁትንና በጆሮዬ የሰማሁትን ቃል ነዉ።Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fighters
ቨርጂኒያ ወደሚገኘዉ “Dulles” አዉሮፕላን ማረፊያ የሄድኩት ከልጄ ጋር ነበር። ከቤቴ Dulles የግማሽ ሰዐት መንገድ ነዉ። ያቺን ግማሽ ሰዐትና አዉሮፕላን ማረፊያ ደርሼ ሻንጣዬን እስካስጭን ድረስ አይኔ እያንዳንዷን ደቂቃ ከልጄ ከቢኒያም አልተለየም። መለየቱን ስላልወደደዉ ልቤ ደንግጧል። ከወያኔ ጋር ለመፋለም በረሃ የሚጓዘዉ ኤፍሬም ከአንድ ልጁ መለየት አቃተዉ። ምነዉ ብዬ እራሴን ጠየኩት- እኔዉ መልሼ ምንም አልኩ። ልጄን አቀፍኩት፤ አሁንም ደግሜ ደጋግሜ አቀፍኩት። እምባ ፊቴን ሞላዉ። ቀና ብሎ ተመለከተኝና ሲከፋዉ ታየኝ። ሁለተኛ ዙር እምባ ፊቴን ሞላዉ። “Son I don’t want to do this, but I have to do it” አልኩ በሁለት እጄ አቅፌ እንደያዝኩት። ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ አባት ሆይ ፈቃድህ ከሆነች ይቺ ጽዋ ከኔ ትለፍ ብሎ የጸለየዉ ፀሎት ትዝ አለኝ። እኛ ሰዎች የዳንነዉ ይህ ፀሎት ባለመመለሱ መሆኑ ትዉስ ሲለኝ ልቤ በሀሳቡ ጸና። አባባ Come on . . . be strong. I promise I will be the son that you raised- you will be proud of me” አለኝ ቢኒያም በዚያ 17 አመት ሙሉ በማዉቀዉ ቆንጆ ድምጹ። የተናገራቸዉ ቃላት ዉስጤ ገብተዉ ኃይል ሲሆኑኝ ተሰማኝ። ጠነከርኩ። ተሰናብቼዉ ወደኋላ እያየሁት ወደ ዉስጥ ገባሁ። ወደ ፍተሻዉ ቦታ ስሄድ ልቤን ከፍተኛ የመለየት ኃዘን እንደ ግግር በረዶ ሲጫነዉ ተሰማኝ፤ መሸከም አቃተኝና እንደ ህፃን ልጅ እያነባሁ ፍተሻዉ መስመር ላይ ገብቼ ወረፋ ያዝኩ።
እንደፈረንጆቹ ዘመን አቆጣጠር ረቡዕ ኦጎስት 5 ቀን ከሌሊቱ 9 ሰዐት የተሳፈርኩበት አዉሮፕላን አስመራ አለም አቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ አይኔ ላይ ዉል ዉል እያለ ልቤን የሰቀለዉ የሚጠብቀኝ የትግል ዉጣ ዉረድ ሳይሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመርቄ በ22 አመቴ ስራ የጀመርኩባት ዉቧ የአስመራ ከተማ ምን ትመስል ይሆን የሚል የሀሳብ ዉጣ ዉረድ ነበር። ሆኖም አካልም መንፈስም እየከዳ ምንም ነገር ማሰብ አይቻልምና ወደ ግዜያዊ ማረፊያ ቦታዬ እንደወሰዱኝ ለሁለት ቀን ከግማሽ የተጠራቀመ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ አለ።
ረቡዕ ከቀኑ አንድ ሰዐት አካባቢ “እባክህ ተነሳና ምሳ እንብላ” የሚል የሁለት ሰዎች ድምጽ ተራ በተራ ጆሮዬ ዉስጥ ገባና እንቅልፌን ሰለበዉ. . . መነሳት ባልፈልግም በልቤ ትግሉ ተጀመረ አልኩና ከተጋደምኩበት ቀና አልኩ። ፊት ለፊቴ ቆመዉ ተነስ እያሉ የሚጨቀጭቁኝ የትግል ጓደኞቼ ነአምን ዘለቀና ብርሀኑ ነጋ ነበሩ። ምሳ ላይ ተቀምጠን እነሱ የሚያወሩት ወደ ኤርትራ በረሃዎች ሰለሚደረገዉ ጉዞ ሲሆን እኔ ደግሞ በወጣትነቴ ስለማዉቃት የአስመራ ከተማ ነበር። አስመራን ትቼ ከነሱ ጋር እንደነሱ ማሰብ ሞከርኩ . . . አሁንም አሁንም ሞከርኩና ሲያቅተኝ ተዉኩት። በተለይ ምሳ የበላንበት ካራቨል ሬስቶራንት ዉስጥ በወጣትነቴ ብዙ ትዝታዎች ነበሩኝና ጭራሽ ምግቡን ትቼ በምናብ ወደ ወጣትነቴ ሽምጥ ጋለብኩ። ባር ኡጎ፤ ባር ቱኔል፤ ባር ፀአዳ ፈርስ፤ ባር እምባባና የባቢሎን ጋጋታ እንዳለ ፊቴ ላይ እየመጡ ተደቀኑ። ቀና ስል ነአምንና ብርሀኑ . . . አትበላም እንዴ አሉኝ። ወደ ኋላ ሽምጥ ያስጋለበኝን ፈረሴን ልጓም ያዝ አደረኩና ካሁን በኋላ ወደፊት ብቻ ብዬ ከሁለቱ ጓደኞቼ ጋር በአካልም በመንፈስም ተቀላቀልኩ።
የአስመራ ከረን መንገድ ከተነጠፈ አስፋልት ዉጭ ሌላ ምንም አይቶ ለማያዉቅ ለእንደኔ አይነቱ የዳያስፖራ ‘በለስ’ ቀርቶ ደጋግሞ የተጓዘበትንም ሰዉ ልብ ይሰልባል። አስመራን ይዞ፤ አዲአቤቶንና እምባደርሆን ይዞ በአዲተከለዛን፤ በኢላበርዕድ፤ በከረንና በሀጋዝ አድርጎ አቆርደት ድረስ የሚዘልቀዉ መንገድ የአለም ተራራዎች ስብሰባ ተጠራርተዉ ወደየመጡበት ላለመመለስ ተማምለዉ የመሸጉበት ቦታ ይመስላል። አንዱን ተራራ ሽቅብ ወጥተንና ቁልቁል ወርደን እፎይ ብለን ሳንጨርስ ሌላዉ ከተፍ ይላል። በስተቀኛችን ያለዉን ተራራ አይተን ወይ ጉድ ስንል በግራችን ያለዉ ድንቄም ጉድ እያለ ያሾፍብናል። እልፍ ስንል ተራራ፤ ከዚያም ተራራ፤ተራራ፤ ተራራ ብቻ ነዉ። ፊት ለፊቴ የማያቸዉ ተራራዎች ተፈጥሮ የቆለለዉ የዲንጋይ ክምር ሳይሆን አዋቂ በዉኃ ልክ እየጠረበ የደረደረዉ ሾጣጣ ኃዉልት ይመስላሉ። አንኳን ለሰዉ ልጅ ለገደሉ ንጉስ ለዝንጀሮም አይመቹም። ባጠቃላይ የአስመራ አቆርደትን መንገድ ሲመለከቱት እንደ አጥር ከተሰለፉት ተራራዎች ባሻገር አገር ያለ አይመስልም። አላማና ጽናት ላለዉ ሰዉ ግን ከተራራዉ ወዲያ አገር ከአገርም ወዲያ ሌላ. . . ሌላ ወያኔ የቀማን አገር አለ።
አላማ የሌለዉ፤ ሆዱ ያልቆረጠ፤ ፈሪ፤ ወኔ የከዳዉና አይኑን ተራራዎቹ ላይ ብቻ ያሳረፈ ሰዉ ከአስመራ ተነስቶ በከረን በኩል አቆርደትን አቋርጦ የጀግኖቹ መንደር ሀሬና የሚደርስ አይመስለዉም። ለዚህ ነዉ ሁሉን የሚችል እግዚአብሄር አይዞህ ብሎ የላከዉ የብሉይ ኪዳኑ ነቢዩ ኤልያስ ኤልዛቤልን ፈርቶ እንደሸሸ ሁሉ የኛም ዘመን ጋዜጠኛ ነን ባዮች፤ ዘፋኞችና አርበኛ ነን ባይ የሀሰት ነቢያት ገና ከረን ሳይደርሱ ተራራዉን እየፈሩ በኤርትራ በኩል ምንም ነገር መስራት አይቻልም እያሉ እንደ ግመል ሽንት የኋሊት የሚጓዙት። ድንቄም ጋዜጠኛ! ጋዜጠኛ ታሪክ ሸራርፎ በሰጠዉ ግዜ እየኖረ ያየዉንና የሰማዉን ለትዉልድ እያስተላለፈ ለራሱ የማይኖር ልዩ ፍጡር ነዉ። የኛዎቹ “ጋዜጠኛ” ነን ባዮች ግን እራሳቸዉ ለራሳቸዉ በሰጡት ግዜ እየኖሩ የራሳቸዉን ግሳንግስ የፈጠራ ታሪክ የሚነግሩን ከህያዉ በታችና ከሙታን በላይ ባለዉ ባዶ ቦታ የሚኖሩ ባዶዎች ናቸዉ። አምላክ በምህረቱ ወደ ላይ ይሳባቸዉና ከህያዋን ጋር ይቀላቅላቸዉ።
ምድረ የወሬ ቋቶች ይግባችሁ! የኢትዮጵያ ህዝብ ዉኃ ዉኃ የሚያሰኝ የእሳት ጉድጓድ ዉስጥ ነዉ ያለዉ፤እሱ ከጉድጓዱ ባስቸኳይ መዉጣት እንጂ እንደናንተ በኤርትራ በኩል ከሆነ ይቅርብኝ ብሎ የሚጃጃልበት ግዜዉም ትዕግስቱም የለዉም። ለነገሩ እነዚህ የወሬ አርበኞች ተራራ ወጥተዉ፤ በረሃ አቋርጠዉና ወንዝ ተሻግረዉ ከወያኔ ጋር ሳንጃ ሊማዘዙ ቀርቶ የገዛ ልጆቻቸውን የልደት ኬክ ደፍረዉ በቢላዋ የማይቆርጡ የ”ዳዉን ታዉን” ቅምጦልች ናቸዉና ከነወሬያቸዉ እዚያዉ “ዳዉን ታወን” ብንተዋቸዉ የሚበጅ ይመስለኛል። አይደል?
ወሬና ስራ ለየቅል ናቸዉ፤ ለወሬ የሚያስፈልገዉ ሹል አፍ ብቻ ነዉ። ለስራ ግን አፍ፤ እጅ፤ አግር፤ አይን፤ ጆሮና የሚያስብ አዕምሮ ያስፈልጋል። ወረኛና ለስራ ያልተፈጠረ ሰዉ የተራራዉ ከፍታ እየታየዉ “በዚህ በኩል እንዴት ተደርጎ” እያለ የወሬ ቱማታዉን መደርደር ይጀምራል። የሚሰራ ሰዉ ግን ግቡ ከተራራዉ ባሻገር ከተከዜ ማዶ ነዉና ተራራዉን ሽቅብ ወጥቶና ከጠመዝማዛዉ መንገድ ጋር እኩል ተጠማዝዞ ወዳለመዉ ግብ ይጓዛል። አንባቢ ሆይ! ሠራተኛ በለኝ አትበለኝ እሱ ያንተ ጉዳይ ነዉ፤ መዳረሻዬ ከተከዜና ከመረብ ወንዞች ባሻገር መሆኑንና አላማዬም ፍትህና ነጻነት መሆኑን ግን እኔዉ እራሴ አብጠርጥሬ ልነግርህ እችላለሁ። የምወደዉን አንድ ልጄንና ጥሩ ስራዬን ደህና ሁኑ ብዬ በረሃ የገባሁት እናት አገሬ ዉስጥ ፍትህ፤ ነጻነት፤ እኩልነትና ዲሞክራሲ አብበዉ ለማየት ነዉ እንጂ የኤርትራ በረሃና ተራራ ናፍቆኝ አይደለም። የናፈቀኝ ተራራና በረሃ ቢሆን ኖሮ አሪዞናና ኮሎራዶ ይቀርቡኝ ነበር።
ዉቧን የአቆርደት ከተማና ቀዳማዊ ኃ/ሥላሤ ያሰሩትን ግዙፍ መስጊድ በስተቀኝ እያየን ወደ ባሬንቱ ስናመራ ያ ከአስመራ ጀምሮ የተከተለን የተራራ መንጋ ፀሐይ እንደገላመጠዉ በረዶ እየሟሸሸ ሄዶ ገና ሀይኮታ ሳንደርስ ሜዳ ሆኖ አረፈዉ። የበረሃዉ ሙቀት እንዳለ ቢሆንም ባሬንቱ ስንደረስ የሚነፍሰዉ ቀዝቃዛ አየር ሙቀቱን አለዝቦታል። ባሬንቱን ለቅቀን ወደ ተሰነይ ስናመራ መሬቱ ሜዳ፤ ሰማዩ ደመናማ፤ አየሩ ነፋሻማ እየሆነ ይመጣል። ትናንሽ ልጆች እዚህም እዚያም ይዘልላሉ፤ ትራክተሩ ያርሳል፤ ግረደሩ ይዳምጣል፤ እንደኔ አይነቱ ጠመዝማዛዉ መንገድ ቀልቡን የሰለበዉና ፀሐዩ ያቀለጠዉ ምስኪን ደግሞ ወላዲት አምላክ ምን በደልኩሽ እያለ ያምጣል። ባሬንቱ ያኔ እኔ ሳዉቃት የጋሽና ሰቲት አዉራጃ ዋና ከተማ ነበረች፤ ዛሬ ከሃያ ስምንት አመት በኋላ ያየኋት ባሬንቱ ግን ከፍተኛ የንግድና የእርሻ እንቅስቃሴ ይታይባታል፤ ዉብትም ስፋቷም በእጥፍ ጨምሯል ፤ደግሞም የዛሬዋ ባሬንቱ የጋሽ ባርካ ዞን ዋና ከተማ ናት።
ከባሬንቱ ወደ ተሰነይ ሲወጣ ግራና ቀኝ አዉራጎዳናዉን ይዞ ኢትዮጵያና ሱዳን ጠረፍ ድረስ የተንጣለለዉ መሬት የኤርትራ የእህል መቀነት ነዉ። አካባቢዉ ከፍተኛ የልማት እንቅስቃሴ ይታይበታል። የኤርትራን ልማትና የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ ማየት የፈለገ ሰዉ ከአስመራና ከሌሎች ትላልቅ ከተማዎች ወጥቶ ገጠር መግባት አለበት። ግድቡ፤ እርሻዉ፤ የጤና ተቋሙና ሌላም ሌላ የመሠረተ ልማት ምልክቶች በጉልህ የሚታዩት ገጠሪቱ ኤርትራ ዉስጥ ነዉ።
ከተሰነይ ወጥተን ጥቂት እንደተጓዝን መኪናችን አስፋልቱን ለቅቃ ኮረኮንቹ መንገድ ዉስጥ ገብታ ስትንገጫገጭ ከእንቅልፌ ነቃሁና እንደመንጠራራት ብዬ . . . ደረስን እንዴ አልኩ … የመኪናችንን ሾፌር። ገና ነዉ ትንሽ ይቀራል አሉ ወደኋላ ዞር ብለዉ። እንዳዉ ለነገሩ ነዉ እንጂ ሰዉዬዉ ዬት እንሄዳለን፤ መቼ አንሄዳለን ወይም መቼ እንመለሳለን ለሚሉ ጥያቄዎች በፍጹም መልስ አይሰጡም። ወያኔ የማይሰማን ሁሉንም ነገር ሆዳችን ዉስጥ ከያዝነዉ ብቻ ነዉ የሚል ፈሊጥ አላቸዉ። ዋናዉን መንገድ ለቅቀን ኮረኮንቹን ከተያያዝነዉ በግምት ከ20 ደቂቃ በኋላ አርበኞች መንደር ቁጥር አንድ ደርስን። ዘፈኑ፤ ጭፈራዉ፤ ሆታዉና ዕልልታዉ ቀለጠ። አርበኛዉ ጠመንጃዉን እንደታቀፈ እየዘለለና እየፎከረ እንኳን ደህና መጣህልን እያለ መሪዉ ላይ ተጠቀለለ። “የወያኔ ዘረኞችና አንዳንድ ተላላዎች አንተንና ጓዶችህን ትኩስ ሀምበርገር እየበላችሁ ወጣቱን በረሃ ዉስጥ ታስጨርሳላችሁ” እያሉ አርበኛዉንና መሪዉን ለመለያየት ብዙ ጥረዋል። እናንተ ግን የሞቀ ኑሯችሁን ትታችሁ ታግላችሁ ልታታግሉን በረሃዉ ድረስ መጥታችሁ ተቀላቅላችሁናል . . . እሴይ የኢትዮጵያ አምላክ! . . . ወያኔ የተሸነፈዉ ዛሬ ነዉ እየለ አርበኛዉ በሆታና በዕልልታ ከዉስጥ የመነጨ ደስታዉን ገልጸ። ብቻ ምን አለፋችሁ ጀግኖቹን ያሉበት ቦታ ድረስ ልናይ ሄደን የጀግና አቀባበል ተደረገልን። እንደ አንድ ታጋይ ድል አፋፍ ላይ ልድረስ አልድረስ አላዉቅም፤ ማሸነፋችንን ግን አረጋገጥኩ።
የነፍስ ወከፍ ጠመንጃዉን እንዳቀፈ ሰላም ሊለኝ ሲመጣ ትኩር ብዬ አየሁት። ወጣት ነዉ፤ ጽናቱና ቁርጠኝነቱ ፊቱ ላይ ይነበባል። በፈገግታ የታጀበዉ የዋህ ፊቱ ልጅነቱን በአዋጅ ይናገራል። ዕድሜዉ ከሃያ አይበልጥም። ተቃቅፈን ሰላም ስንባባል እጅብ እጅብ ብሎ የተጎነጎነ ፀጉሩን በእጄ እያሻሸሁ “እቺን ነገር ታበድረኛለህ” አልኩት ፀጉር እየከዳዉ ያስቸገረኝን እራሴን እያሳየሁት። ችግር የለም አለኝ። “ችግር የለም” በአርበኞቹ ሠፈር የተለመደ አባባል ነዉ። የበረሃዉ ንዳድ፤ የዉኃዉ ጥማት፤ የምግብ ችግር፤ ክብደት ተሸክሞ ተራራዉን ሽቅብ መዉጣትና ባጠቃላይ ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን ማስወገድ ለአርበኛዉ ችግር አይደለም። አርበኛዉ ለእንደነዚሀ አይነት ችግሮች ተዘጋጅቶ ስለመጣ እንደችግር አይመለከታቸዉም።
ድንኳን ዉስጥ ገብተን ቁጭ እንዳልን . . . . እዚህ አካባቢ ችግራቸሁ ምንድነዉ አልኩት። ይምጡ አለኝና ከድንኳኑ ይዞኝ ወጥቶ ገዢ መሬት ይዘዉ የመሸጉትን የተለያዩ ካምፖች አሳየኝና የእያንዳንዳቸዉን ስም ነገረኝ። ሁላችንም የመጣነዉ ከኢትዮጵያ ነዉ፤ ሁላችንም የምንታገለዉ ወያኔን ነዉ፤ ደግሞም የሁላችንም ጥያቄ ፍትህ፤ ነጻነትት፤ እኩልነትና ዲሞክራሲ ነዉ. . . .. ግን አንድ ላይ አንታገልም። እስከመቼ ነዉ የአንድ አገር አርበኞች ከአገራችን ወጥተን፤ የተለያየ ድንኳን ተክለን፤ በተናጠል የጋራ ጠላታችንን የምንዋጋዉ? እባካችሁ ገላግሉን ብሎኝ ቀና ሲል አይኑ ካይኔ ገጠመ። በአፉ ከነገረኝ በአይኑ የነገረኝ በለጠብኝ። እንዲህ አይነቱን ብስለት የተሞላዉ ንግግር የሰማሁት ከልጄ ብዙም ከማይበልጥ ኢትዮጵያዊ ወጣት መሆኑ ሲሰማኝ እራሴን ታዘብኩት፤ ኢትዮጵያዊነቴን ግን ከወደድኩት በላይ ወደድኩት። አዎ አሁንም አሁንም አትዮጵያዊነቴን ከነችግሩ ወደድኩት። ደግሞስ ዬኔ ስራ ችግር መፍታት ነዉ እንጂ የአገሬ ችግር ፊቴ ላይ በተደቀነ ቁጥር ኢትዮጵያዊነቴን ጥያቄ ዉስጥ ማስገባት አይደለም።በነገራችን ላይ በተናጠል የሚደረገዉ ትግል አያዋጣምና “እባካችሁ አንድ አድርጉን” የሚለዉ ጥያቄ የአንድ አርበኛ ጥያቄ ሳይሆን በየሄድኩበት ካምፕ፤ ግምባርና ምሽግ ዉስጥ ከአብዛኛዉ አርበኛ አፍ የሚወጣ ጥያቄ ነዉ።
ቀኝ እጄን ወጣቱ አርበኛ ግራ ትከሻ ላይ አሳረፍኩና በሌባ ጣቴ በርቀት የሚታዩትን ካምፖች እያሳየሁት… አንዱጋ መሄድ እንችላለን አልኩት። አይ ጋሼ አሁን መሽቷል አለኝ። ሰዐቱ ገና ከቀኑ 9 ሰዐት ቢሆንም ሰፈሩ የአርበኞች ስለሆነ በነሱ ህግ መተዳደር አለብኝ ብዬ እሺ አልኩት። አይዞት እናንተ አስተባብራችሁ አንድ አድርጉን እንጂ ሌላ ሌላዉ ችግር የለዉም አለኝ። እኔም እንደ ወጣቱ አርበኛ በድፍረት “ችግር የለም” ለማለት ባልደፍርም . . . አይዞህ ትብብርን በተመለከተ በቅርብ ግዜ ሁላችንንም የሚያስደስት ዜና አብረን እንሰማለን አልኩት። ፈገግ አለና እሱን ከጨረሳችሁልን ሌላዉን ለኛ ተዉት አለኝና ይዞኝ ወደ ድንኳኑ ገባ።
ሐሙስ ነኃሴ 13 ቀን ጎህ ሳይቀድ ከእንቅልፌ ተነሳሁና ትንሽ ዞር ዞር ብዬ አልጋዬ ላይ ተመልሼ መጽሐፌን ማንበብ ጀመርኩ። ሁለት ምዕራፍ ጨርሼ ሦስተኛዉን ልጀምር ስል ከሩቁ ቡና ቡና ሸተተኝ። ቀና ብዬ ስመለከት ፍረወይኒ የቆላችዉን ቡና እስከነማንከሽከሻዉ ተሸክማ ልታስሸትተኝ ስትመጣ አየኋት፤ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቁርስ ደረሰ እንዴ ብዬ ማንከሽከሺያዉ ላይ የሚንቦገቦገዉን ጭስ በእጄ ደጋግሜ ወደ አፍንጫዬ ሳብኩት። ‘ኡወ ቁርሲ ደሪሱ’ ብላ ፍረወይኒ የተቆላዉን ቡና ይዛ ወደ መጣችበት ተመለሰች።
ከጧቱ አንድ ሰዐት ከመሆኑ በፊት ቁርስ ተበልቶ አለቀና ሁላችንም ወደየተመደብንበት መኪና እንድንገባ ተነገረን። የሚጸዳዳዉ ተጸዳድቶ ሲጋራ የሚያጤሰዉም ሲጋራዉን ለምጦ ጉዞ ተጀመረ። ዬት እንደምንሄድ ወይም ለምን እንደምንሄድ የጠየቀም የተናገረም አልነበረም። . . . ዋ! ትንፍንሽ ብትሉ የተባለ ይመስል ሁሉም አፉን ዘግቶ ወደማያዉቀዉ ቦታ ጉዞዉን ቀጠለ። አንድ ሰዐት ያክል እንደተጓዝን . . . “እነዚያ ቤቶች ይታዩሃል” የሚል ድምጽ መኪናዉ ዉስጥ የሰፈነዉን የዝምታ ጽላሎት ሰበረዉ።አዎ ይታየኛል . . . ምን የምትባል ከተማ ናት ብዬ ቀና ስል ትልቅ ወንዝ አየሁ፤ ግን ወንዙንም ከተማዉንም ስለማላዉቃቸዉ ምንም አልተሰማኝም። እንድያዉም ፀሐይ ያጋለዉን ሰዉነቴን ለማቀዝቀዝ ወደ ወንዙ እንሂድ አልኳቸዉ። “ይቅርብህ እንደቀዘቀዝክ ትቀራለህ” አለኝ ከአጃቢያችን አንዱ።
ከተማዉ ኦምሀጀር፤ ወንዙ ተከዜ፤ ከወንዙ ባሻገር የሚታየዉ ከተማ ደግሞ ሁመራ መሆኑ ሲነገረኝ . . . የምን ወንዝ መዉረድ እዚያዉ ቀዝቅዤ ቀረሁ። አደራ ቦቅቧቃ እንዳትሉኝ . . . አልፈራሁም አልደነገጥኩም። በእርግጥ እንኳን እንደዚያ ቀርቤዉ ከሩቅ ከባህር ማዶም ጠልፎ ሊወስደኝ የሚፈልግ ሰላቢ የነገሰበትን ምድር ሳላዉቀዉ እንደዚያ በድንገት መቅረቤ ትንሽም ቢሆን አሳስቦኛል። ይልቅ እንደዚያ ያፈዘዘኝና ገና ወንዙ ዉስጥ ሳልገባ ያቀዘቀዘኝ እናት አገሬን ኢትዮጵያን በ25 አመት ለመጀመሪያ ግዜ ማየት መቻሌ ወይም የእናት ኢትዮጵያ ናፍቆት ነዉ። ለነገሩ አገርም ሰዉም የሚናፍቀዉ ርቀዉ ሲሄዱ ነዉ። ዬኔ ናፍቆት ግን ልዩ ጭራሽ ልዩ ነዉ። አጠገቧ ቆሜ አገሬ ናፈቀችኝ። አዎ! መግቢያዬ ቀረበ መሰለኝ ኢትዮጵያ ስቀርባት ይበልጥ ናፈቀችኝ።
በቃ አንሂድ አለ ይዞን የመጣዉ የበላይ መኮንን . . . አዎ እንሂድ እንጂ ከዚህ በላይ መቆየት ለወያኔ ካልሆነ ለሌላ ለማንም አይበጅም አሉ ሌላዉ በዕድሜ ጠና ያሉ የበላይ መኮንን። እኚህ ሰዉ የወያኔ ስም ሲነሳ ደማቸዉ ይፈላል ፤ እሳቸዉ እራሳቸዉ እንደ ዳዊት ሲደጋግሙት ግን ምንም አይሰማቸዉም። ከሰዐት በኋላ ረፋዱ ላይ ሁላችንም ወደየመኪናችን ገብተን ኦምሀጀርን ለቅቀን ወደ ጀግኖቹ አገር ወደ ሀሬና አቀናን። ሀሬና አርበኞች ግንቦት 7ን፤የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄን፤ የአማራ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄን፤ የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ድርጅትንና ደምህትን ወላድ ማህፀንዋ ዉስጥ አምቃ የያዘች እርጉዝ ምድር ናት። እርግጠኛ ነኝ በቅርቡ ትወልዳለች።
የአስመራ ምፅዋ መንገድ እንደ ጥምጥም እየተጠመጠመ እየቀናና እየጠመመ ለረጂም ሰዐት የሚዘልቅ ያዋቂንም የልጅንም ቀልብ የሚሰልብ ሰላቢ መንገድ ነዉ። እግዚኦ . . . የከረን መንገድ በስንት መልኩ! ከአስመራ ምፅዋ መሄድ ማለት ከ2500 ሜትር ተራራ ላይ ቁልቁል ወርዶ ባህር ወለል መድረስ ማለት ነዉ። ትንፋሼን ቋጥሬ በቀኜ ገደሉን በግራዬ ተራራዉን እያየሁ ለሰዐታት ቁልቁለቱን ከተያያዝኩት በኋላ የቋጠርኩትን ትንፋሽ አዉጥቼ እፎይ ማለት የጀመርኩት ማይ አጣል ስደርስ ነዉ። ከማይ አጣል በኋላ ምፅዋ ድረስ መንገዱ ሜዳ ነዉ።
ምፅዋ ልንደርስ ትንሽ ሲቀረን ሆዴን ባር ባር አለዉ። የደስታ ይሁን የሀዘን ወይም የሲቃ አላዉቅም ብቻ ልቤ ሌላ ሌላዉን ሰዉነቴን ትቶ ደረቴ ዉስጥ ብቻዉን ይዘላል። “ዉስጥ እጄን ይበላኛል” ምን ሊያሳየኝ ይሆን . . . ይል ነበር የልጅነት ጓደኛዬ። ምነዉ እኔም እንደሱ ሆኜ ዉስጥ እጄን በበላኝ . . . ልቤ ደረቴን ጥሶ የሚወጣ እሰኪመስል ድረስ ደረቴ ዉስጥ ከሚዘል። አይፎኔን አወጣሁና ግራና ቀኙን አይኔ ያረፈበትን ቦታ ሁሉ ፎቶ አነሳሁ። ቦታዉ ዶጋሌ ይባላል. . . አዎ! ዶጋሌ . . . ጀግናዉ ራስ አሉላ 500 የጣሊያን ወታደሮችን ዶጋ አመድ ያደረጉበት የድል ቦታ። ለካስ ልቤ አለምክንያት አልዘለለም! ጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ዉስጥ የአምስት መቶዎቹ አደባባይ የሚባል ቦታ አለ (ፒያዛ ዴ ቺንኮ ቼንቶ)። እመኑኝ እኛም አገር አይቀርም! ባንዳ ባንዳዉንና ልክ ልኩ ሲነገረዉ ደንግጦ የሞተዉን ምናምንቴ ሁሉ ትተን ሞተዉ ህይወት የሆኑልንን የትናንትናና የዛሬ ጀግኖቻችንን እናስታዉሳለን።
ምፅዋ ሁለት ቀን ብቻ ነዉ ያደርኩት – ቅዳሜና እሁድን። በጦርነቱ የፈራረሱ ህንጻዎች አሁንም አልፎ አልፎ ይታያሉ፤ ያም ሆኖ ምፅዋ ዉብ ከተማ ናት፤ ደግሞም አያሌ አዳዲስ ህንጻዎች ተሰርተዉባታል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ጠ/መምሪያ የነበረዉ ማዕከል ግን በጦርነቱ እንደፈረሰ ነዉ፤ ያየዉም የነካዉም ያለ አይመስልም።
እሁድ ነኃሴ 16 ቀን ከምፅዋ ተነስተን 45 ደቂቃ ከነዳን በኋላ ዊሃ ደርስን። ዊሃ ሌላዉ የአርበኞች መንደር ነዉ። ዊሃ ያለዉ አርበኛ እንዴት እንደተቀበልን ለመግለጽ አማርኛ ቋንቋ እንደገና “ሀ” ብዬ መጀመር የሚኖርብኝ ይመስለኛል። በዚያ የወፍ ማረፊያ በሌለበትና በየሴኮንዱ ዉኃ ዉኃ በሚያሰኝበት ንዳድ ዉስጥ ወታደራዊ ሥልጠና መዉሰድ ቀርቶ አንድ ሜትር መራመድም እጅግ በጣም ይከብዳል። እንግዲህ ይታያችሁ የኛዎቹ ጀግኖች እንደዚህ የምድር ሲኦል በመሰለ ቦታ ነዉ ወገኖቻቸዉን ከወያኔ መንጋጋ ነፃ ለማዉጣት እልህ አስጨራሽ የሆነ ወታደራዊ ሥልጠና የሚወስዱት። እኔም የኢትዮጵያን ህዝብ ከወያኔ ዘረኞች ለማላቀቅ እንደወያኔ 17 አመት ጫካ ለጫካ መንፏቀቅ እንደሌለብን ቁልጭ ብሎ የታየኝ ዊሃ ሄጄ እነዚህን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ስመለከት ነዉ።
ሰኞ ነኃሴ 17 ቀን በጧት ተነስተን ጉርጉሱም ሄድን። ጉርጉሱም ቀይ ባህር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ቆንጆ የመዋኛ ቦታ ነዉ። ቁርስ አዝዘን ሳንጨርስ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ከተፍ አለ። ታጋይ ሞላ በድንገት አልነበረም የመጣዉ፤ ልክ በቀጠሮዉ ሰዐት ነበር የደረሰዉ። አብሮን ቁርስ በላና እኛ ቀይ ባህር ዉስጥ ገብተን ስንምቦጫረቅ እሱ ማይ አጣል እንገናኝ ብሎ መኪናዉን አስነስቶ ከነፈ።
ከጥዋቱ 11፡30 ሲሆን ዋናችንን ጨርሰን የምፅዋ አስመራን መንገድ ተያያዝነዉ። ከምፅዋ አስመራ ጉዞ ማለት ሽቅብ ወደሰማይ የሚደረግ ጉዞ ማለት ነዉ፤ እንደኔ አይነቱ የዋህ ሰዉ ሰማዩን ደርሶ በእጁ የሚነካ ይመስለዋል ፤ ግን ሰማዩም ሞኝ አይደለም ደረስኩብህ ሲሉት ይሸሻል። ከቀኑ 12፡30 ሲሆን ማይ አጣል ደረስንና አስፋልቱን ትተን ወደ ደምህቶች ካምፕ የሚወስደዉን የኮረኮንች መንገድ ተያያዝነዉ። ወደ ካምፑ ስንደርስ ዊሃን፤ ሄሬናን፤ አምሀጀርንና ሌሎቹንም የአርበኞች ግንቦት 7 ካምፖች ስንጎበኝ ያየነዉ ፍጹም ኢትዮጵያዊ የሆነ የእንግዳ አቀባበል ተደረገልን። በነገራችን ላይ የደምህቶችን ካምፕ ስንጎበኝ ይህ የመጀመሪያችን አይደለም። ለእግራችን ዉኋ ቀረበልንና ነጠላ ጫማ ያደረገዉ ሁሉ እግሩን በቀዝቃዛ ዉኃ አራሰዉ። ቀዝቃዛ ዉኋ ለእግር ማቅረብ በሁሉም አርበኞች ካምፕና በበረሃዉ የኤርትራ ክፍል የተለመደ ባህል ነዉ። ከቀኑ እንድ ሰዐት ሲሆን ምሳ ቀርቦ እየተበላ ቡና ይፈላ ጀመር። ረከቦቱ፤ጀበናዉ፤ ማቶቱ፤ የከሰል ምድጃዉ፤ ፈንዲሻዉና የተደረደረዉ ስኒ በቀጥታ ወደ አደኩበት ሠፈሬ ፒያሳ ወሰደኝ። አዎ! ፒያሳ… የአዲስ አበባዉ ሳይሆን የአዋሳዉ ፒያሳ።
ቡናዉ እየተጠጣ ጨዋታዉ ሞቅ ሲል ቆየት ካሉት የጥላሁን ገሠሠ ሙዚቃዎች አንዱ ከሩቅ በለሆሳስ ተሰማኝ። በዉኔ ነዉ በህልሜ ብዬ ቀና ስል ነአምን ዘለቀ ጥላሁንን ከቴፑ ጋር አብሮ ይጫወታል። በህልሜ አለመሆኔን አወቅኩት። በሞት የተለዩን ድምጻዉያን የኛዎቹም የዉጮቹም ከላይ ከሰማይ ቢጫወቱልን እርገጠኛ ነኝ ጋላክሲዉንና ናሳ “Black Hole” እያለ የሚነግረንን ዬትየለሌ ክስተት አቋርጦ ከፀሐይ ብርሐን ቀድሞ እኛጋ የሚደርሰዉ ዘመን አይሽሬዉ የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ብቻ ነዉ። ይህንን ስሜት የሚኮረኩር፤ ጅማት የሚወጥርና አዕምሮን ሰብስቦ በትዝታ የሚያስዋኝ ዉብ ቃና ነበር ደምህቶች ሲያሰሙን የዋሉት። ብቻ ምን ልበላችሁ. . . ወበቅ የተቀላቀለዉ የምፅዋ ንዳድ ሳይቀር ለጥላሁን ገሠሠ ሙዚቃ ቦታዉን ለቀቀ። እኛም ወታደራዊ ትዕዛዝ የተሰጠን ይመስል የሁላችንም አፍ ተዘግቶ የሚንቀሳቀሰዉ እግራችን፤ ትከሻችንና ጭንቅላታችን ብቻ ሆነ።
“አልማዝን አይቼ እልማዝን ሳያት”፤ “እንጉዳዬ ነሺ” “አመልካች ጣት” “መሳቁን ያስቃል” . . . ብቻ ምን አለፋችሁ የጥላሁን ሙዚቃ ተዥጎደጎደ። ጥላሁን ገሠሠ አስመራ ላይ የሚጠብቀንን ቀጠሮ ብቻ ሳይሆን ጭራሽ እኛነታችንን አስረሳን። ቢበዛ አንድ ሰዐት ብለን የመጣን ሰዎች ከሦስት ሰዐት በላይ ከደምህት ጓዶቻችን ጋር ቆየን። በመጨረሻ የጉዟችን መሪ “አንድ ለመንገድ” ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ። እሱ ሲነሳ “እንክርዳድ እንክርዳድ የተንከረደደ፤ ስንዴ መስሎ ገብቶ ስንቱን አሳበደ” የሚለዉ ዘፈን እያለቀ ነበር። ነአምን. . . ነአምን ብዬ ስጣራ . . . “One for the road” ይቀረናልኮ አለ ነአምን . . . እንሂድ የምለዉ መስሎት። ይህንን ሙዚቃ እንደ እንክርዳድ ተቀላቅሎን ለሚያሳብደን የዳያስፖራ ቱልቱላ መርጫለሁ አልኩት። ሳቅ አለና ከቴፑ ጋር መጫወቱን ቀጠለ። እርግጠኛ ነኝ ተቦርነ በየነ ወይም መሳይ መኮንን አንድ ቀን “እንክርዳድ እንክርዳድን” በኢሳት ያሰሙናል። አይደል ተቦርነ?
በመጨረሻ የኛም መሄጃ የሙዚቃዉም መገባደጃ ደረሰ። “One for the road” የተባለለት ሙዚቃ (ዘፈን) ገና ሲጀምር ሰማሁና ኢችንማ አምላክ ነዉ የመረጠልን አልኩ በልቤ። ያ በቁሙ “አጥንቴም ይከስከስ” ብሎ ያስተባበረን ጥላሁን ገሠሠ አሁንም ከላይ ከሰማይ ቤት “ቃልሽ አይለወጥ እባክሺ….ን” እያለ ቃል እንድንገባባ አደረገን። ተራ በተራ ከአርበኛ ሞላ አስገዶም ጋር እየተቃቀፍን “ቃልሽ- አይለወጥ- አባክሽን” ብለን ተለያየን። ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ ብዬ ነበር የጀመርኳችሁ፤ አሁንም ቃሌ ይሄዉ ነዉ። ቃላችን አይለወጥ! ቸር ይግጠመን።
ኤፍሬም ነኝ ከአርበኞች መንደር
ebini23@yahoo.com

Saturday, August 29, 2015

የቤተመንግስት ደህንነት ሃላፊ ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

የቤተ-መንግስት የደህንነት ጥበቃ ዋና ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት የሕወሐት አባል አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ምንጮች አስታወቁ። አቶ ጌታቸው ቀደም ሲል በክልል 14 ፖሊስ ኮሚሽን የደሕንነት ልዩ ተወርዋሪ ሃይል ሃላፊ ተደርገው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ከዚያም ወደ ቤተ መንግስት ተዛውረው መመደባቸውንና በተጨማሪ የአገር ውስጥ ደህንነት ምክትል ሃላፊ በመሆን ከአቶ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን አስረድተዋል። የአቶ መለስና ወ/ሮ አዜብ የቅርብ ሰው የሆኑት አቶ ጌታቸው ተፈሪ በነበራቸው ታማኝነት የቤተመንግስት የደህንነት ሃላፊ ተደርገው በአቶ መለስ ተመርጠው እንደተሾሙ ያስታወሱት ምንጮች፣ በማያያዝም እስከ 1994ዓ.ም የቤተመንግስት የደህንነት ጥበቃ በሃላፊነት ሲመሩ የቆዩት አቶ ዘርኡ መለስ በወቅቱ ከአቶ መለስ ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ልይነት ምክንያት ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ “ኮከብ ሬስቶራንት” የአሁኑ “ሚልክ ሃውስ” መኖሪያ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ ቤታቸው ውስጥ አንገታቸው በስለት ታርዶና በድናቸው ተበላሽቶ መገኘቱን አመልክተዋል።

34


ይህን አሰቃቂ ግድያ ያከናወነው አሁን በእስር ቤት የሚገኘው የቀድሞ አገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊና የአቶ መለስ ቀኝ እጅ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል መሆኑን ምንጮቹ አጋልጠዋል። አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣን እንዲነሱ የተደረገው በደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ ትእዛዝ መሆኑን ያመለከቱት ምንጮች፣ በአሁኑ ወቅት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ እንደማይታወቅ ጠቁመዋል። አቶ ጌታቸው ተፈሪ የወ/ስላሴ መታሰር ቅር ሳያሰኛቸው እንዳልቀረና በተጨማሪም የነአዜብ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል።

Guddaa saalpaa fariddi guniddaan dhessa “ኦሮሚያን እንገነጥላለን የሚለው ጥያቄ ታላቋ ኢትዮጵያን ለመሰረተው የኦሮሞ ህዝብ ስድብ ነው” በፍቃዱ ኃይሉ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

“ኦሮሚያን እንገነጥላለን የሚለው ጥያቄ ታላቋ ኢትዮጵያን ለመሰረተው የኦሮሞ ህዝብ ስድብ ነው” በፍቃዱ ኃይሉ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ አውሮፓውያን አፍሪካን ለመቀራመት ተሰብስበው ወሰኑ፡፡ ኃያላኑ መንግስታት የየድርሻቸውን ሲወስዱ የኢትዮጵያን አካባቢዎች ለመውረር የሞከረው የጣሊያን መንግስት ነበር፡፡ አውሮፓውያን ወራሪዎች ‹‹ዓላማችን አፍሪካውያንን ከእንቅልፋቸው ቀስቅሶ ማሰልጠን ነው›› ቢሉም እየዋሹ ነበር፡፡ ዋነኛ ዓላማቸው የአፍሪካን ሀብት ለፋብሪካዎቻቸው ጥሬ ዕቃ ማድረግ ነበር፡፡ ሆኖም እግረ መንገዳቸውን አፍሪካውያንን ሀይማኖታቸውን እያስለወጡ ከራሳቸው ጋር ያመሳስሉታል፡፡ ቋንቋ፣ ወግ እና ልማዶችን በማጥናት ዘመናዊ በሚሉት በራሳቸው ቋንቋ፣ ወግ እና ልማድ ይተኩታል፡፡ አፍሪካውያንን ማሰልጠን የሚሉት ይህንን ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ከቅኝ ግዛት በኋላ ብዙ አፍሪካውያን የራሳቸውን ቋንቋ፣ ባህል እና ስርዓት ሙሉ ለሙሉ አጥተው በአውሮፓውያን ገዥዎቻቸው ባህል እና ስርዓት እየተዳደሩ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ግን በአንጻሩ ይህንን ወረራ በኅብረት መመከት በመቻሏ ምንም እንኳን ከአውሮፓ ተጽዕኖ ባትተርፍም የተለየ (የራሷን) ባህል እና ወጎችን እንደያዘች አለች፡፡


በፍቃዱ ኃይሉ

ኢትዮጵያ የአውሮፓ ወራሪዎችን መመከት የቻለችው ህዝቦቿ በመተባበራቸው ነው፡፡ የጣልያን ሰራዊት አድዋ ላይ ድል ካደረጉት የጦር መሪዎች መካከል ባልቻ ሳፎ (በፈረስ ስማቸው አባ ነፍሶ) ሳይጠቀሱ የማይታለፉ የኦሮሞ ልጅ ናቸው፡፡ ከምንም ተነስተው የጦር ሚንስትር እስከመሆን የደረሱት ሀብተጊዎርጊስ ዲነግዴ (አባ መላ) ለዚህ ደረጃ የበቁት በአድዋ ባሳዩት ጀግንነት እና መለኝነት ነበር፡፡ እርሳቸውም የኦሮሞ ልጅ ናቸው፡፡ ጣልያን ድል ሆኖ መመለሱ ቆጭቶት ከ40 አመታት በኋላ ሲመለስም ወረራውን በመመከት ረገድ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ኦሮሞዎች ተሰልፈው ነበር፡፡ ከነዚህም መካከል የማይዘነጉት እነ ገረሱ ዱኪ እና ጃጋማ ኬሎ ይገኙበታል፡፡ ጀግናው ጃጋማ ኬሎ ፍቀረማርቆስ ደስታ በጻፈላቸው ታሪካቸው ውስጥ ‹‹ኦሮሞ የኢትዮጵያ ግንድ ነው›› ሲሉ ነግረውታል፡፡ እውነታቸውን ነው፡፡

የኦሮሞ ህዝብ በብዛት ትልቁ ኢትዮጵያዊ ብሄረሰብ ነው፡፡ የኦሮሞ ታሪክ ከተጻፈው በላይ ትልቅ ነው፡፡ የኦሮሞ ጎሳዎች ይተዳደሩበት የነበረው የገዳ ስርዓት ዴሞክራሲ ለኦሮሞ ህዝብ ባህሉ ነው ያስብላል፡፡ በኦሮሞ ባህል የሰዎች አደረጃጀት የበላይና የበታች የሚለው ብዙም ተቀባይነት የለውም፡፡ በየትኛውም የገዳ ስርዓት የስልጣን እርከን ላይ ያለን ሰው የትኛውም ተራ ሰው መተቸት እንዲችል የኦሮሞ ባህል ይፈቅድለታል፡፡ ይህ ዓይነቱ ባህል የህዝብ መሪዎች ከህዝብ ትችት እንዳያመልጡ የሚያደርግ ስለሆነ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ያስፈልገናል፡፡
የኦሮሞ ህዝብ፣ ምንም እንኳን የብዛቱን ያህል ተጠቃሚ ባይሆንም የኦሮሞ ልጆች በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የስልጣን ተቀናቃኝ ሆነው አልፈዋል፡፡ አንዳንድ ባለታሪኮች ‹ዘመነ መሳፍንት› የሚሉት የኢትዮጵያ ክፍለ ታሪክ በየጁ ኦሮሞዎች ኢትዮጵያ የተመራችበት ዘመን ነው ይላሉ፡፡ ያኔ መናገሻ የነበረችው ጎንደር ከተማ የስራ ቋንቋዋ ኦሮምኛ ሆኖ ነበር፡፡ በሌላ ጊዜ ደግሞ ንግስናውን ያገኙት የአማራ እና የትግሬ ገዢዎች ከኦሮሞ ጦረኞች ጋር ተስማምቶ ለማደር በጋብቻ መተሳሰርን መርጠዋል፡፡ ለምሳሌ ቴዎድሮስ ልባቸው እስኪጠፋ ያፈቅሯት የነበረችው ሚስታቸው የወሎው ኦሮሞ ራስ አሊ ልጅ ተዋበች ነበረች፡፡ አጤ ምኒልክ ያገቡት ‹‹የኢትዮጵያ ብርሃን›› የምትባለውን ዜደኛ የየጁ ኦሮሞ ሴት ጣይቱ ብጡልን ነበር፡፡ …ኦሮሞዎች ኢትዮጵያን በቀጥታ ባልገዙበት ዘመን በተዘዋዋሪ አዝዘውባታል፡፡

በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንዳለመታደል ሆኖ ህዝቡ ተመችቶት አልኖረም፡፡ የኦሮሞ ህዝብም የዚሁ ገፈት ቀማሽ ነበር፡፡ መሪዎች በተገላበጡ ቁጥር ለራሳቸው ሲሉ ድሃውን ገበሬ ሲያንገላቱ ኖረዋል፡፡ ነገስታቱ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ከጎናቸው ያልተሰለፈውን ሁሉ በኃይል ያጠቁ ነበር፡፡ ገበሬው ያመረተውን ቆርሶ የማካፈል ግዴታ ነበረበት፡፡ ግብር የበዛባቸው ገበሬዎች ከመማረራቸው የተነሳ የእህል ክምራቸውን የንጉስ ወታደሮች ሊወስዱባቸው ሲመጡ እህሉ ላይ እሳት ለኩሰውበት ይሸሹ ነበር፡፡ ነገስታት በመጡ፣ ነገስታት በሄዱ ቁጥር ድሃው ህዝብ እረፍት ሳያገኝ ኖሯል፡፡ የኦሮሞ ህዝብ ከጥቂቶቹ የስልጣን ተቀናቃኞች በስተቀር ቀሪው ያሳለፈው ታሪክ የፈተና ነበር፡፡ ሆኖም ግን ጭቆናው ዴሞክራሲያዊ (ህዝባዊ) ያልሆኑ መንግስታት ባሉበት ቦታ ሁሉ ብዙሃኑ ላይ የሚጫን ቀንበር ነው፡፡

የኦሮሞ ህዝብ በታሪኩ ባደረጋቸው እንቅስቃሴዎች ከደቡብ ወደ ሰሜን በመስፋፋት ያልሰፈረበት የኢትዮጵያ ግዛት የለም፡፡ ከሁሉም ህዝብ ጋር ተቀላቅሏል፡፡ በአንዳንድ ቦታዎች የራሱን ባህልና ቋንቋ ሲያወርስ በሌሎች ቦታዎች ደግሞ ከተስፋፋባቸው አካባቢዎቹ የቀድሞዎችን ነዋሪዎች ባህልና ቋንቋ እንዲሁም ሀይማኖት ወርሷል፡፡ ‹‹ግማሽ ሲዳማ››፣ ‹‹ግማሽ ጉራጌ›› የሲዳማንና የጉራጌን ባህል የወረሱ ኦሮሞዎች ናቸው፡፡ የወሎ ኦሮሞዎች አማርኛ ቋንቋ እና እስልምና ሀይማኖት ወርሰዋል፡፡ ራያ እና አዘቦዎች ትግርኛ ቋንቋና ክርስትናን ወርሰዋል፡፡ … በዚህ መንገድ ኦሮሞዎች ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ተሳስረዋል፡፡ ሶሾሎጂስቱ ዶናልድ ሌቪን የኦሮሞዎች እንዲህ ከሌሎች የመዋሃድ ችሎታ ትልቋን ኢትዮጵያ ፈጥሯል ይላሉ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝቦች አሁንም ከገዥው ጭቆና አልተላቀቁም፡፡ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ልክ እንደ ትላንቷ ኢትዮጵያ የመብት ጥያቄ ያነሱ ልጆች በኃይል ይጨፈለቃሉ፡፡ ይህንን ጭቆና ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች በየራሳቸው መንገድ እየታገሉት ነው፡፡ ይሁን እንጂ በተባበረ ክንድ መታገል ባለመቻላቸው ጭቆናው ሊቆም አልቻለም፡፡ ብዙ የኦሮሞ ልጆች መፍትሄው የኦሮሚያ መገንጠል እንደሆነ ሊያምኑ ይችላሉ፡፡ ኦነግ በቀድሞው ብርታቱ ባይኖርም መንፈሱ አለ፡፡ ብዙዎች የኦነግ መንፈስ የሚሉት ይህንን ‹‹እንገነጠላለን›› የሚለውን ጥያቄ ነው፡፡ ብዙዎች የተሰውለት፣ ብዙዎች የታሰሩለት፣ ብዙዎች የተሰደዱለት ጥያቄ ይሄው ቢሆንም እስካሁን ለውጥ አላመጣም፡፡ በእኔ እምነት ጥያቄው ለውጥ ያላመጣው በሁለት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ ትልቋን ኢትዮጵያ የመሰረተው የኢትዮጵያ ግንድ (የኦሮሞ ህዝብ) እንደቅርንጫፍ እገነጠላለሁ ማለቱ ነበር፡፡ ሁለተኛ ጠላታችን የሆነውን ጭቆና ማሸነፍ የምንችለው በመተባበር እንጂ በመለያየት ባለመሆኑ ነው፡፡

የጣልያን ወረራን ያሸነፍነው በተባበረ ክንዳችን እንጂ በተነጣጠለ ኃይል አይደለም፡፡ አሜሪካ ዓለምን የምትመራው ክፍለ ሀገሮቿ ተባብረው አንድነት ስለቆሙ ነው፡፡ አውሮፓውያን የአውሮፓ ህብረትን የመሰረቱት የአሜሪካን ኃያልነት በህብረት ለመቋቋም ነው፡፡ አፍሪካም ወደ ህብረት እየሄደች ነው፡፡ በህብረታችን ታሪካዊ ጠላታችን ጭቆናን ማሸነፍ ይቻላል፡፡ መገነጣጠል ግን ይብሱን ያደክመን ይሆናል እንጂ አይበጀንም፡፡ የኤርትራ መገንጠል ለኤርትራ ህዝብ ነጻነት አላስገኘም፡፡ የደቡብ ሱዳን መገንጠል ለደቡብ ሱዳናውያን ሰላም አላመጣላቸውም፡፡ የሶማሊያ አንድ ብሄር መሆንና አንድ ሀይማኖት መከተል ከመበጣበጥ አላዳናቸውም፡፡ መዋጋት ያለብን ጭቆናን እንጂ ህብረታችንን አይደለም፡፡
ኦሮሚያን እንገነጥላለን የሚለው ጥያቄ ታላቋ ኢትዮጵያን ለመሰረተው የኦሮሞ ህዝብ ስድብ ነው፡፡ ሽንፈት ነው፡፡ ትግሉ መሆን ያለበት ጠንካራና ነጻ ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ ነው፡፡ የኦሮሞ ፖለቲከኞች ለዚህ ዓላማ (ሌሎች ፖለቲከኞች ባይመቿቸው እንኳ) የዴሞክራሲ ባህላቸውን ተጠቅመው ሊታገሉት ይገባል እንጂ የገነቧትን ትልቋን ኢትዮጵያ ጥለው እንገነጠላለን ማለት የለባቸውም እላለሁ፡፡ የታላቅነት ምስጢሩ ህብረት እንጂ ነጠላነት አይደለም፡፡ በህብረት እናሸንፋለን!


Guddaa saalpaa fariddi guniddaan dhessa

Befqadu Hailu

Dhumnii jaarraa kudha saglaffaa dhuma yeeroo Awuroopaanoonnii ardii Afrikaa hirachuuf murtteeffatan ture. Mootootnii awuuroopaa kan ga’ee isaanii yoommuu fudhatan, ga’een Xaaliyaanii naannawa Itiyoophiyaa tuuree.Weerartoonnii Awuroopha sababni weerarreef ‘’ummata Afrikaa hirriba irra damaqsiinee qaroomsuufii’’ yoo jedhan illee dhugaan yeeroo sanaa garuu kanarraan adda.Sababnii weeraraa innii guddaan omisha warshaaleetif meeshaa dheedhii argachuu dabrees gabaa barbaaduuf ture. Amantaa Afrikaanoota jijjiraa gocha fakkoo isaanii taasisuus walfaana raawwatuu.Afaan, aadaa fi duudhaa ummatichaa eega qoratanii booda afaan, aadaa duudhaa ammayyaa dha jedhaniii amannan kan offii uwwisuu tuuree.Egaa Afrikaa qaroomsuu kan jedhan gocha akkanaa kanaan.Sababa gocha awuroopaanoota kanaan biyootnii Afrikaa baayyeen afaan,aadaa,duudhaa ofii guutumaan guutuuttii dhabanii enyummaa gita bittootaatin buluttiideemaniruu. Gama kanaan Itiyoophiyaan dhibbaa awuroopaanoota irra hafuu baattuus, hamma tokko aadaa fii dhudhaa adda ta’ee qabbattee turuu dandessee jirtii.

Itiyoophiyaan weerartoota Awuroophaa qolachuu dandessuun ishee tuumsa ummattotaa walirrattii godhaniini.Injifanno aduwaa loola Xaaliyaani wajjin godhamee irrattii shoorrii ijoolleen oromo kana akka Baalchaa Safoo maqa fardaatiin Aba Nafsoo taphatan akka laayyootii kan ilaalamu mitii.Sababnii Fiit Awraarii Habta Giyoorgisi Dinagdee (abba malaa) sadarkaa hoggansaa abbaa duulaa ga’uun isaanii innii guddaan jagnummaa adda waraana aduwaa irrattii raawwataniin turee. Xiiqii waggaa afuurtamaatiin Xaaliyaan deebi’ee biyyattii yoommu weeraruu, qabsoo bilisa baasaa Itiyoophiyaa fiiniinsuu kessattii, Itiyoophiyaanoota kaan wajjiin hinkoo isaanii bahanii jiruu. Gama kanaan Garasuu fi Jaagamaa maqaa kaasuun ni danda’ama. Jaagamaa keelloo Gootichii, kitaaba seena dhunfaa Fikira Maarkoosi Dastaa barreesseefi kessattii ‘’dame malee Jirmiii hin binxamuu’’ jedhanii ibsaniruu.Jeechi isaanii kuun dhugaa turee.
Saboota biyyattiin qabduu keessaa Oromoon lakkofsaan guddaa dha.Seenaan Oromoo seenaa barraayee jiruu irrayyuu guddaa dha.Sirnii ittin bulmaata Oromoo, Sirni Gadaan, dimookraasiin Oromoof aadaa akka ta’ee kan mullisuu dha. Sadarkaa hawaasa wajjin walqabatee Aadaa Oromoo kessattii guddaa fi xiqqa jeedhanii qooduun hin jiruu. Sirna gadaa kessattii nama sadarkaa hoggansa kamuu qeequun aadaa oromootii.Aadaan akkasii kuun bakka buutoonni ummata qeeqa ummataa miliquu akka hindandeenyee taasisa waan ta’eef ummanni Itiyoophiyaa biraatiifisi muxxannoo irra fayyadamuu qabanii dha.

Ummannii Oromoo hamma baayyina isaa fayyadamoo ta’uu baatuus, ijoolleen Oromoo angoo siyaasa Itiyoophiyaa argachuuf falmaa darbaniruu. Beektootnii siyaasa tokko tokko kutaa seenaa biyyattii ‘’Zamana Masaafinti’ jedhamee yeeroo beekamuttii biyyattiin Oromoo yajjuu jala bulaa akka turtee nii ibsuu.Yeeroo kanattii afaan masaraa Goondari afaan Oromoo akka turee seenaan nii ibsa.Gama biraatiin yoo ilaallee mootootni Amharaa fi Tigree looltota Oromoo wajjin fuudhaafi heerumaan firummaa horatanii falmii angoo siyaasa hambisuu tuuree. Intaltii Mootii Teewoodrosijaalalaan boojitee intala Oromoo Wollo Raas Alii kantaatee Tawaabachi turtee. Kana qofaa mitii.Nitii Mootii miniliki ‘’Ibsituu Itiyoophiyaa’’ jedhamtee jajamtuu xaayituu bixuuli dubara Oromoo yajjuu dha.Bara Oromoonnii Itiyoophiyaa hin bulchinee kessattii ilee murtee karra dubaan dabruu kessattii qooda qabuu tuuree.

Akka carraa ta’ee seenaaItiyoophiyaa keessattii yeeroon ummannii jireenya mijoo dabarfatee hin turree.Ummannii Oromoos dararoo kana dhandhamatee jira.Bulchitoonnii yoommuu jijjiraman fedha isaanitiif jecha qootee bulaa dhippisuu turee.Mootootnii biyyattii ummata isaan faana hin hirirree tarkaanfii humnaan gutamee fudhatuu.Callaa Qootee bulaan omisheemootii bulchuu wajjiin dirqama qoduu qaba tuuree.Qootee bulaa gibira kafaluu dadhabee ijjii isaa otoo arguu looltoonii motichaa omisha isaa akka hin fudhanne calla dafqa isaatiin omishee gubee baqataturee .Mootin tokko dabreee mootiin biraa yoo dhufuu ummanni boqonnaa dhabaatii kan jiraatee.Namoota muraasa angoof dhama’an malee jiruun ummannii dabarsee jiruu deegaa turee. Haata’uu malee Cunqursaan akkasii kuun waanjoo gabrummaa bakka bulchaan ummataa kara dimookraatawaatiin hin filamnee marattii kan fe’amuu dha.

Baballina ummatnii Oromoo Seena kessa raawwateen kaaba fi kibba biyyattii keessattii bakka ummannii Oromoo hin qubannee hin jiruu.bakka tokko tokko afaanii fii aadaa isaa barsiisaa bakka birattii immoo aadaa fi afaan akkasumas ammanta bakka sanaa dhaalee jiraata. “Walakkaa sidaama” fi “walakkaaguuraageen” warra aadaa sidaama fi guraagee fudhatanii dha.Oromoon woolloosi afaan Amhaara fi amanta Islaamaa fudhataniruu.Raayyaa fi Azaboon Tigriffa fi kiristaanummaa fudhataniruu. Gama kanaan ummannii Oromoos ummattoota Itiyoophiyaa kaan wajjin walittii hidhinsa umee jiraa.Soosiyoolojistii Donaald Leevan jedhaman akka ibsanittii amala dafanii ummata biraa wajjin makamuu oromoon qabutuu Itiyoophiyaa gudittii uumee jedhu.

Ammas taanan ummannii Itiyoophiyaa gita bittaa cunqursitoota jala hin baanee.Itiyoophiyaan harraa akka Itiyoophiyaa kalessa san bakka nammoonni mirgasaani gaafatan humnaan ukkaamamanii dha. Itiyoophiyaanoonni hundii Cunqursaa kana karaa filataniin qabsaa’atii kan jiran. Haata’uu malee ummannii tokkummaan ka’ee cunqursaa kana ofiirraa qolachuu waan hin dandeenyeef cunqurfamuun hin hafnee.Ijoolleen Oromoo baayyeen fallii kana foxxoquu dha jedhuu ta’a. Jabina duraan qabuu haa dhabuu malee afurrii ykn miirrii ABO ammas jira.Namoonnii baayyeen afurrii ABO afura ‘’foxxoquu dha‘’ jedhanii amanuu.Namoonnii hedduun galma kanaaf wareegamani, hidhamani biyya irra baqataniis jijjiramnii barbaadamuu hin dhufnee. Akka hubannoo kiyya yoo ta’ee sababnii galmii kun hin ga’iniif sababa lamaanii. Sababni inni Tokkoffaan jirmii Itiyoophiyaa hundessee (ummatnii oromoo) akka dameettii binxama jechuu isaatinii.lammaffaan dina keenya kan ta’ee cunqursaa mo’uu kan dandeenyuu walin dhaabbachuun malee adda bahani waan hin taaneefii dha.
Weerara xaaliyaanii qolachuun kan danda’amee irree gamteessuutini malee qabsoo dhunfaatiin hin turree.Ameerikaan addunyaa dursaa kan jirtuu kutaaleen biyyaa walin waan dhaabbatanifii. Dhiibbaa Ameerikaa dandamachuuf Awuroopaanoonnii gamtaa Awuroophaa hundessani jiruu.Afrikaanisi gamtaa ykn tokkummaa Afrikaattii deemaa jirtii.Tokkummaa keenyaan dina seenaa kessa kan ta’ee cunqursaa mo’uu ni danda’ama.Adda bahuun garuu sirumaa humna nuu dhabsisa malee nuu hin toolu.Foxxooquun Eritriyaa ummataaf bilisummaa hin fidnee.Foxxoquu Sudaan Kibbaatin nagaa horachuun hin taane.Saba tokko ta’uunifii amantaa tokkoo hordoofuun ummata Soomaaleetiif waa hin buusnee .Kan looluu qabnuu cunqursaamalee tokkummaa ykn gamtaa keenyaa ta’uu hin qabu.

Ummata Itiyoophiyaa hundesseef Oromiyaa foxxoqsina gaaffiin jedhuu arraba. Mo’amuu dha.Qabsoon kan ta’uu qabuu Itiyoophiyaa bilisaafii cimtuu dhugoomsuu dha. Hayyootiin siyaasa Oromoo(hayyulee siyaasa biro wajjin wali galuu baatanis) aadaa dimookraasii qabanittii fayyadamanii qabsaa’uu qaban malee biyyaa Itiyoophiyaa ijaarree dhisnee foxxoqna jeechuu hin qaban.Iccitiin haangafumma tokkumaa ykn gamtummaa dha malee addaan bahuu mitii.Injifannoon keenyaa gamtaa keenyaanii!

Sudan Calls for Redrawing of Borders with Ethiopia


Border demarcation has been Ethiopia’s source of conflict with Sudan and Eritrea
Border demarcation has been Ethiopia’s source of conflict with Sudan and Eritrea for long time now. Ethiopians accuse Sudanese forcesfor illegally occupying their land while Eritreans accuse Ethiopia for the same
The governor of Sudan’s Gedaref state, Merghani Salih, has called for redrawing of borders between Sudan and Ethiopia in order to bring the long running dispute between the two nations to an end.
Farmers from two sides of the border used to dispute the ownership of land in the Al-Fashaga area located in the south-eastern part of Sudan’s eastern state of Gedaref.
The two governments have agreed in the past to redraw the borders, and to promote joint projects between people from both sides for the benefit of local population. However, the Ethiopian opposition has used to accuse the ruling party of abandoning Ethiopian territory to Sudan.
In November 2014, Sudan’s president Omer al-Bashir and Ethiopian premier, Hailemariam Desalegn, instructed their foreign ministers to set a date for resuming borders demarcation after it had stopped following the death of Ethiopia’s former prime minister, Meles Zenawi.
Also, in December 2013 the Joint Sudanese- Ethiopian Higher Committee (JSEHC) announced that it reached an agreement to end disputes between farmers from two sides of the border over the ownership of agricultural land particularly in the Al-Fashaga.
Salih on Friday emphasized to a federal delegation from the societal and popular police currently visiting Gedaref the need to redraw the Sudanese-Ethiopian borders in order to end land disputes permanently.
He pointed to the importance of the joint military patrols to secure the borders between the two countries, praising the role of the societal and popular police in protecting the borders.
It should be mentioned that Al-Fashaga covers an area of about 250 square kilometers and it has about 600.000acres of fertile lands. Also there are river systems flowing across the area including Atbara, Setait and Baslam rivers.
Sudan’s Gadarif and Blue Nile states border Ethiopia’s Amhara region. The borders between Sudan and Ethiopia were drawn by the British and Italian colonizers in 1908.

ስኳር ኮርፖሬሽን በዚህ አመት 7 ቢሊዮን ብር ኪሳራ ደረሰበት

ኢሳት ዜና (ነሐሴ 22 ፣ 2007) ከአራት አመት በፊት የተቋቋመውና አስር የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታ ለማካሄድ ሃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን በተጠናቀቀው የ 2007 አም በጀት አመት የሰባት ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደደረሰበት ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። የሃገሪቱ ነባር የስኳር ፋብሪካዎች እንዲያስተዳድር ሃላፊነት ተሰጥቶት የነበረው ይኸው ኮሮፖሬሽን ለስራው ማስኬጃ ከተለያዩ የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር ለእቃ አቅርቦት መከፈል የነበረበትን ሶስት ቢሊዮን ብር በወቅቱ ሳይከፍል መቅረቱን ታውቋል። የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ካጋጠመው ከፍተኛ ኪሳራ በተጨማሪ አቶ አባይ ጸሃዬ ኮሮፖሬሽኑን ለሁለት አመታት ያህል በዳይሬክተርነት ባስተዳደሩበት ጊዜ ከ 800 ሚሊዮን ብር በላይ የደረሰበት እንዳልታወቀ የድርጅቱ ምንጮች ለኢሳት በሰጡት መረጃ አመልክተዋል። የተከሰተውን የገንዘብ ጉድለት ተከትሎም የድርጀቱ የቦርድ ሊቀመንበር የሆኑት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ አብተው ጉዳዩን ለጠቅላላ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ቢሮ በማቅረብ የኦዲት ምርመራ እንዲካሄድ ጥያቄ ማቅረባቸው ታውቋል። ይሁንና ጥያቄ የቀረበለት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ለጉዳዩ ምላሽ አለመስጠቱን የተናገሩት ምንጮች ለስኳር ኮርፖሬሽኑ ያጋጠመውን የፋይናንስ ቀውስ ተከትሎም በርካታ ሰራተኞች ከድርጅቱ በመልቀቅ ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል። በአቶ አባይ ጸሃዬ ምትክ ሃላፊ ሆነው የተሾሙት አቶ ሽፈራው ጃርሶ በተለያዩ መድረኮች “ የተረከብኩት በቁሙ የሞተ ድርጅት ነው” ሲሉ መግለጻቸውም ተነግሯል። ቅሬታቸውን በማቅረብ ላይ የሚገኙት አቶ ሽፈራው ጃርሶ በቅርቡ የስራ መልቀቂያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት እንዲያቀርቡ የኮርፖሬሽኑ ምንጮች ለኢሳት አስረድተዋል። የግንባታ ስራዎች በተጋነነ ዋጋ ያለጨረታ መሰጠታቸውና ከተሰጡም በኋላ የዋጋ ልዩነት መጥቷል እየተባለ በድጋሚ የተጋነነ ክፍያ ሲፈጸም በመቆየቱ ኮሮፖሬሽኑ በኪሳራ ውስጥ ከተካተቱ ድርጅቶች ዋነኛው መሆኑን ከምንጮች ለመረዳት ተችሏል። የቀድሞው የኮሮፕሬሽኑ ዳይሬክተር የነበሩት አቶ አባይ ጸሃዬ የባለቤትነት ድርሻ አላቸው የሚባለውና በቀድሞ GYB ቡቲክ ባለቤት አቶ የማነ ግርማይ የተሰጠው እና ኦሞ በሚገኘው የኩራዝ ስኳር ፋብሪካ ግንባታ በተጋነነ ዋጋና ያለጨረታ ከተሰጡ ግንባታዎች መካከል ምሳሌ መሆናቸውን ምንጮች ማስረጃዎችን በማስደገፍ ለኢሳት አመልክተዋል። ኮርፖሬሽኑ ለሌሎች ኩባንያዎች ክፍያን መፈጸም እንዳማይችል ቢገለጽም ይኸኛው ግንባታ ግን ክፍያ ተቋርጦ እንደማያውቅበት ለመረዳት ተችሏል። የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስካሁን የተበደረው ብድር መጠን 44 ቢሊዮን ብር መድረሱን የገለጹት ምንጮች፣ ድርጅቱ ተጨማሪ ካፒታል ካልተመደበለት የመፍረስ አደጋ ሊገጥመው እንደሚችል አስታውቀዋል። ኮርፖሬሽኑ ለሚዋዋላቸው የተጋነኑ ውሎችና ስምምነቶች ብድሩን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲያገኝ መቆየቱም ታውቋል።

በቃሉ ወረዳ አንድ ሰው በታጣቂዎች ተገደለ

በቃሉ ወረዳ አንድ ሰው በታጣቂዎች ተገደለ
ነኅሴ ፳፪ (ሀያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ወሎ ዞን በቃሉ ወራዳ ጅጋ ቀበሌ ላይ ጀማል ሙሼ የተባለ የ22 ዓመት ወጣት፣ ሃምሌ 27 ቀን 2007 ዓም በሚሊሺያዎች ተገድሏል። ወጣት ጀማል ሙሼ በዩ፣ ሰይድ ሙሄ ጌሮና እንድሪስ ኡመር በተባሉ ታጣቂዎች ተገድሎ ከአካባቢው 24 ኪሎሜትር ርቆ ሊቀበር ሲል መረጃ የደረሳቸው ዘመዶቹ ቦታው ድረስ በመሄድ አስከሬኑን ወስደዋል። ወጣቱ ግንባሩ አካባቢ በጥይት የተመታ ሲሆን፣ ሁለቱ ኩላሊቶቹም ወጥተዋል። ታጣቂዎቹ ወጣቱን ብረታብረት እንሸጥልሃለንና 40 ሺ ብር ይዘህ ና ብለው እንዳስመጡት፣ ነገር ግን ቦታው ደርሶ በዋጋ ለመስማማት አለመቻሉን ዘመዶቹ ለኢሳት ተናግረዋል። ሌሎች ጉደኞቹ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ ታጣቂዎቹ ጀማልን መንገድ ላይ በማስቆም በጥይት ገድለው ገንዘቡንና የእጅ ስልኩን ይዘው በመሄድ ለመቅበር ሲሞክሩ ዘመዶቹ ደርሰዋል። ታጣቂዎቹ እንዲያዙ ዘመዶቹ ለመንግስት አቤት ቢሉም የሚሰማቸው ማጣታቸውንና ገዳዮቹ አሁንም ድረስ ስራቸውን እየሰሩ መሆኑን አለም ይወቅልን ሲሉ ቤተሰቦቹ ተናግረዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የወረዳውን ባለስልጣናት ለማናገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።


Friday, August 28, 2015

የማኅበረ ቅዱሳን ንዋያተ ቅድሳት ማምረቻ ክፍል ቃጠሎ ደረሰበት

የማኅበረ ቅዱሳን ንዋያተ ቅድሳት ማምረቻ ክፍል ቃጠሎ ደረሰበት
ነሐሴ 21 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
01 kateloበማኅበረ ቅዱሳን የልማት ተቋማት አስተዳደር የንዋያተ ቅድሳት ማምረቻ ክፍል ነሐሴ 18 ቀን 2007 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ቃጠሎ እንደደረሰበት የልማት ተቋማት አስተዳደር ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ ፍስሐ ገለጹ፡፡

መረጃው ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት እንደደረሳቸው የገለጹት አቶ ኃይሉ በማምረቻ ክፍሉ ተከስቶ የነበረውን ቃጠሎ በአካባቢው ሕዝብና በአዲስ አበባ ከተማ አራዳ ወረዳ የእሳት አደጋ ማጥፊያና መቆጣጠሪያ ክፍል አባላት ርብርብ ወደ ሌሎች ክፍሎች ሳይዛመት በቁጥጥር ሥር እንዲውል መደረጉን ተናግረዋል፡፡

በቃጠሎው 12 የልብስ ስፌት ማሽኖች፤ 2 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ካውያዎች፤ 1 መዘምዘሚያ ማሽን፤ 1 ቁልፍ መትከያ ማሽን፤ በዝግጅት ላይ የነበሩና ያልተጠናቀቁ፤ ለስፌት የሚያገለግሉ የግሪክ ጨርቆች፤ የካህናት፤ የዘማርያንና የሰባኪያን አልባሳት፤ ለአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተዘጋጁ አልባሳት፤ የግሪክ ጣቃ ጨርቆች፤ የማምረቻ ክፍሉ በሮች፤ መስኮቶችና ኮርኒስን ጨምሮ ሙሉ ለሙሉ ወድመዋል፡፡ ግምታቸውንም ለጊዜው ማወቅ እንዳልተቻለ ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

02kateloበዕለቱ ቀኑን ሙሉ መብራት ጠፍቶ ስለነበር ምንም ዓይነት ሥራ አገልጋዮቹ እንዳለከናወኑ የገለጹት ዳይሬክተሩ ቃጠሎው የተከሰተው አገልጋዮቹ ከወጡ በኋላ በመሆኑ የአደጋው መንስኤ እሰካሁን አለመታወቁን ተናግረዋል፡፡ አደጋው የተከሰተበት ምክንያት ፖሊስ የቴክኒክ ምርመራ በማካሔድ ላይ ስለሚገኝ ምርመራው እንደተተናቀቀ የሚታወቅ ይሆናል ብለዋል፡፡

ወደፊት ጥንቃቄ የተሞላበት ሥራ ለማከናወን ጥረት እንደሚደረግ የገለጹት አቶ ኃይሉ ከኢንሹራንሽ ጋር በተያያዘም ወደፊት የሚሠሩ ሥራዎች እንደሚኖሩ ጠቁመዋል፡፡ በቃጠሎው ከፍተኛ ጉዳት ሳይደርስ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ላደረጉ አካላት ለአራዳ ክፍለ ከተማ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መቆጣጠሪያ ጣቢያ፣ ለአካባቢው ምእመናንና ፖሊስ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በንዋያተ ቅዱሳት ማምረቻ ውስጥ የአልባሳት፤ የመባ /ዕጣን፤ ጧፍ፤ ዘቢብ/ ዝግጅት፤ የተማሪዎች አልባሳት፤ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉና በእንጨት የሚዘጋጁ ንዋያተ ቅድሳት እንዲሁም የብረታ ብረት ሥራዎች ይመረታሉ፡፡

source http://eotcmk.org/site/-mainmenu-18/1969-2015-08-27-12-32-39

የሰማያዊ ፓርቲ ኣባል አቤል ኤፍሬም ጓደኞቹ እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ላይ የአቃቤ ህግ ምስክር ሆኖ ቀረበ



በእነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ላይ የአቃቤ ህግ ምስክር ተሰማ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የኢትዮ-ኤርትራ ድንበርን አቋርጠው ኤርትራ የሚገኘውን ግንቦት ሰባት የተባለ በተወካዮች ም/ቤት ሽብርተኛ የተባለ ድርጅትን ሊቀላቀሉ ሲሄዱ ተይዘዋል በሚል የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ላይ የአቃቤ ህግ ምስክር ተሰማ፡፡
ዛሬ ነሀሴ 22/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት አንደኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ ሁለተኛ ተከሳሽ እየሩሳሌም ተስፋው፣ ሦስተኛ ተከሳሽ ፍቅረማርያም አስማማው እንዲሁም አራተኛ ተከሳሽ ደሴ ካህሳይ ‹‹አቃቤ ህግ በጻፈውና ለተከሳሽ በደረሰው የክስ ማመልከቻ ላይ አቃቤ ህግ የሰው ማስረጃ (ምስክር) አልጠቀሰም፤ እኛም መቃወሚያ ስናስገባም ሆነ እምነት ክህደት ቃል ስንሰጥ ይህን ግምት ውስጥ በማስገባት ነው፤ በመሆኑም የአቃቤ ህግ ምስክር ሊሰማብን አይገባም›› በሚል ተቃውሞ ቢያቀርቡም አቃቤ ህግ ለፍርድ ቤቱ ባስገባው ክስ ላይ ምስክሩን መጥቀሱን በማስረዳት ምስክሩ እንዲሰሙለት ጠይቋል፡፡
ፍርድ ቤቱ የደረሰው የክስ ማመልከቻ ላይ ምስክር እንደተመዘገበ በማረጋገጥም ብቸኛ ሆነው የቀረቡትን አንድ የአቃቤ ህግ ምስክር ሰምቷል፡፡ ምስክሩም ከ1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሰሾች ጋር ሰማያዊ ፓርቲ በሰላማዊ ትግል ውስጥ ሆነው እንደሚተዋወቁ፣ የካቲት 12/2007 ዓ.ም በ1ኛ እና 2ኛ ተከሳሽ አማካኝነት ሰላማዊ ትግሉ እንዳላዋጣ በመጥቀስ ግንቦት ሰባትን ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ መጓዝ ማሰባቸውን ገልጸውለት በዚያው ቀን ማታ 3ኛ ተከሳሽን ጨምሮ ወደ ባህር ዳር እንደተጓዙ ለችሎቱ አስረድቷል፡፡
ባህር ዳር ሲደርሱ ጠዋት ላይ ግን ምስክሩ ሀሳቡን በመቀየር ወደ አዲስ አበባ መመለስ እንደሚፈልግ እንደገለጸላቸው፣ 1ኛ ተከሳሽ በበኩሉ ‹ጎንደር ላይ የምናገኘው ሰው ስላለ ቢያንስ እሱን ካገኘኸው በኋላ መመለስ ትችላለህ› እናዳለው፣ ነገር ግን ምስክሩ በሀሳቡ ባለመስማማት ወደ አዲስ አበባ መመለሱንና ሌሎቹ ሦስቱ ግን ጉዟቸውን መቀጠላቸውን አስረድቷል፡፡ ‹‹ባህር ዳር ላይ ለምን ለመመለስ ወሰንህ›› የሚል መስቀለኛ ጥያቄ ከ1ኛ ተከሳሽ የቀረበለት ምስክሩ፣ ‹‹በወቅቱ ስሜታዊ የሚያደርጉ የግል ጉዳዮች ስለነበሩብኝ በስሜታዊነት የወሰንኩት ውሳኔ በመሆኑ ነው›› ሲል ተናግሯል፡፡
ምስክሩ ‹‹ለምስክርነት ያስገደደህ አካል የለም ወይ›› ተብሎ ሲጠየቅ ‹‹የለም›› የሚል መልስ ሰጥቷል፡፡ ‹‹ግንቦት ሰባት ነጻ አውጭ ድርጅት ነው ወይስ አሸባሪ›› ተብሎ በተከሳሾች መስቀለኛ ጥያቄ ተነስቶ፣ አቃቤ ህግ ተቃውሞውን በማሰማት ‹‹ድርጅቱ በተወካዮች ም/ቤት አሸባሪ ተብሏል፡፡ ይህ የህግ ጉዳይ ነው›› በማለት ጥያቄውን ምስክሩ የመመለስ ግዴታ እንደሌለባቸው አስረድቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም ይህን ተቃውሞ ተቀብሎ ምስክሩ ጥያቄውን እንዲያልፉት ተደርጓል፡፡ ‹‹ማዕከላዊ ታስረህ ነበር፣ ድብደባም እንደደረሰብህ በሚዲያ ሳይቀር ተዘግቧል፡፡ ልክ ነው?›› ተብሎ በመስቀለኛ ጥያቄ ሲጠየቅ ምስክሩ ‹‹ማዕከላዊ ቃል እንድሰጥ ተደርጌያለሁ፤ ግን አልታሰርኩም›› የሚል መልስ ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ የምስክሩን ቃል ከሰማ በኋላ የአቃቤ ህግን አስተያየት የጠየቀ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ የምስክሩ ቃልና የሰነድ ማስረጃውን መርምሮ ፍርድ ቤቱ ብይን እንዲሰጥለት ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ብይኑን ለማሰማት ለመስከረም 5/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

የአርበኞች ግንቦት 7 መልዕክት ለሆዳም የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት

መልዕክት በድሆች ድህነት ለመክበር መሯሯጥ ላይ ላሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት !

የግል ኑሮን ለማደላደል ሲባል የወያኔ አባል መሆን “ወይን ለመኖር” የሚል ስያሜ ከተሰጠው ዓመታት ተቆጥሯል። “ወይን ለመኖር” ዜጎች ነፃነታቸውን ለጥቅም አሳልፈው የሚሸጡበት፤ የሰው ልጅ ክብር የሚዋረድበት ገበያ ነው። በወይን ለመኖር “የገበያ ህግ” መሠረት እያንዳንዱ ዜጋ ሊያገኘው መብቱ የሆነውን አገልግሎት እንዲያገኝ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴግ፣ የደህዴግ፣ የአብዴፓ፣ የቤጉህዴፓ፣ የጋህአዴን፣ የሀብሊ ወይም የኢሶዴፓ አባል መሆን፤ አልያም መደገፍ ግዴታ ነው። እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች የህወሓት ተቀጽላ ወያኔዎች ናቸው። የእነዚህ ድርጅቶች አባል ወይም ደጋፊ ያልሆነ እንኳስ የመንግሥት አገልግሎት ሊያገኝ ጥሮ ግሮ ያፈራውንም ይነጠቃል።
በዚህም ምክንያት፣ በገጠር ያለው አርሶ አደር ቁራጭ የእርሻ መሬት፣ የግብርና ባለሙያዎች የምክር እገዛ፣ የማዳበሪያና ዘር ግዢ፣ ብድር ወይም እርዳታ ለማግኘት በአካባቢው ባለ የወያኔ ድርጅት አባልነት መመዝገብ፤ አንድ ለአምስት መደራጀት እና የወያኔን የስልጣን እድሜ የሚያራዝሙ ነገሮችን መሥራት ይጠበቅበታል። በከተሞች ውስጥም ሥራ ለመቀጠር፣ ለደረጃ እድገት፣ የመኖሪያ ቤት (ኮንዶሚንየም) ለመግዛት ሲባል መወየን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ሆኗል:: በንግዱም ዘርፍ የንግድ ፈቃድ፣ የሥራ ቦታ እና የባንክ ብድር ለማግኝት፣ የመንግሥት ጨረታዎችን ለማሸነፍ፣ ከጉምሩክ እቃ ለማስለቀቅ፣ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት መወየን ግዴታ ነው።
“ወይን ለመኖር” የኢትዮጵያን ሕዝብ ያዋረደ፤ ለትውልድ የሚተርፍ የማኅበራዊ ስነልቦና ኪሳራ ያደረሰ እና ደካማውን ወያኔን ጠንካራ በማስመሰል በሕዝብ የትግል መንፈስ ውስጥ ፍርሃትን የረጨ መሆኑ ግንዛቤ እየዳበረ በመጣ መጠን እየቀነሰ የመጣ ክስተት ነው። በአሁኑ ሰዓት ከቀድሞው እጅግ በተሻለ ኢትዮጵያ ውስጥ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ራሳችንን ከህወሓት ባርነት እያላቀቅን ምሬታችንን በግልጽ መናገር የጀመርንበት ወቅት ነው፤ ከዚያም አልፎ የህቡዕ ተግባራዊ የትግል እንቅስቃዎችን ማድረግ ደረጃ ላይ ደርሰናል።
አገር ውስጥ እየተዋረደ የመጣው “ወይን ለመኖር” በአገዛዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካይነት በውጭ አገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን (ዲያስፓራ) መካከል ነፃነታቸውን በጥቅም የሚለውጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ፍለጋ ተሠማርቷል። አገዛዙ ተስፋ ያደረገው ያህል ባይሆንም ጥረቱ የተወሰነ ውጤት እያስገኘለት ነው። በጥቅማ ጥቅም እየደለለ ካመጣቸው ውስጥ በስርዓቱ ብልሹነት ያዘኑና የተሰማቸውን በግልጽ የተናገሩ መኖራቸው የሚያስደስትና የሚያበረታታ ቢሆንም ከመንደር ካድሬዎች ባነሰ ተለማማጮችና አጎብዳጆች በማየታችን ተሸማቀናል። ኢትዮጵያ ውስጥ ካለነው አብዛኛው ሕዝብ አንፃር ሲታይ በተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙት ዲያስፓራዎች መካከልም ነፃነታቸውን በጥቅም ለመለወጥ የሚፈቅዱ መገኘታቸው አሳዛኝ ነው። እነዚህ ክብራቸውን በጥቅም የለወጡ ዲያስፓራዎች ዓለም ባንክንና የዓለም የገንዘብ ድርጅትን (IMF) ተክተው ህወሓት ስላስገኘው ፈጣን እድገት በአገዛዙ ራድዮ እና ቴሌቪዥን ሲነግሩን መስማት ያሳፍራል። የህወሓት አገዛዝ “ፍትህን፣ መልካም አስተዳርንና ዲሞክራሲን አስፍኗል፤ ይህንንም መጥተን በዓይኖቻችን ተመልክተናል” እያሉ የግፉን ገፈት እየቀመስን ላለነው ሲነግሩን መስማት ያማል።
እነዚህ ወገኖቻችን ህወሓትን በማሞካሸት የሚያገኙት መሬት ብዙ ድሆች የተፈናቀለቡት፤ ለእነሱ በብላሽ የተሰጠው ብድር በረሃብ ለሚጠቃ ወገን የተላከ እርዳታ መሆኑ ማሳሰብ ይገባል። ከህወሓትና አጫፋሪዎቹ ጋር ተስማምተው ባገኙት ገንዘብ የሚቆርሱት እያንዳንዱ እንጀራ የብዙ ወገኖቻችን ደምና እንባ የፈሰሰበት መሆኑ ማስገንዘብ ያሻል። ከህወሓት ጋር በማበር በወገኖቻችን ድህነትና ችጋር እየከበሩ ያሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት ከዚህ እኩይ ሥራቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቅ ይገባል። እኚህ ወገኖች የራሳቸው ክብር ማጉዳፋቸውን ብቻ ሳይሆን የልጅ ልጆቻቸውም የሚያፍሩባቸው መሆኑን ማስታወስ ይገባል። ከዚህም አልፎ የዛሬ ተግባራቸው ነገ በህግ የሚያስጠይቃቸው መሆኑን ሊያውቁ ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የአገዛዙን እድሜ በማራዘም ላይ የተሰማሩ፤ በድሆች ድህነት ለመክበር በመሯሯጥ ላይ ያሉ፤ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ለአገዛዙ ጥብቅና የቆሙ የዲያስፓራ አባላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳስባል።
አርበኞች ግንቦት 7 “ከህወሓት ውድቀት በኋላ ያለው ጊዜ ለእናንተም ከዛሬው የተሻለ ይሆናል። ዛሬ ከህወሓት ጋር ያላችሁን ሽርክና አቋርጡ። ለነፃነት የሚደረገውን ትግል እርዱ፤ መርዳት ባትችሉ እንቅፋት አትሁኑ፤ አለበለዚያ ግን ከተጠያቂነት የማታመልጡ መሆኑን እወቁ” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!! !

ፍርድ ቤቱ አቶ ማሙሸት አማረ በነፃ እንዲቀለቀቅ ወሰነ

ፍርድ ቤቱ አቶ ማሙሸት አማረ በነፃ እንዲቀለቀቅ ወሰነ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የአራዳ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ነሃሴ 22/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም መንግስት ከጠራው ሰልፍ አንድ ቀን ቀድሞ ከለቅሶ ቤት ወደ ቤተ መንግስት የተደረገውን ሰልፍ አደራጅቶ መርቷል እንዲሁም ለዋናው (ለሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም) ሰልፍ አነሳስቷል በሚል ክስ የተመሰረተበት አቶ ማሙሸት አማረ በነፃ እንዲለቀቅ ወስኗል፡፡
አቃቤ ህግ ነሃሴ 20/2007 ዓ.ም አቶ ማሙሸት ገንዘብ ከፍሎ ወጣቶችን ሰልፍ እንዳስወጣቸው፣ ወጣቶችን እንዳደራጀ፣ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅትም መንግስትን የሚተቹ መፈክሮችን በመሪነት ሲያሰማ እንደነበርና ለሚያዝያ 14 ሰልፍም ሲያደራጅ እንደነበር ያስረዱልኛል ያላቸውን ሶስት የሰው ምስክሮችን ማሰማቱ ይታወሳል፡፡
ይሁንና ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግ ምስክሮች የግል ሰራተኛ እንደሆነ በምስክርነት ቃላቸው ቢሰጡም በመስቀለኛ ጥያቄ አንደኛው የመንግስት ሰራተኛ፣ ሁለተኛው የወጣቶች ሊግ ከዚህም አለፍ ሲል የኢህአዴግ አባል፣ ሶስተኛው ደግሞ የጥቃቅንና አነስተኛ ባልደረባ መሆናቸውን በማመናቸው የሰጡት ምስክርነት ትክክል አለመሆኑን ያስረዳል ብሏል፡፡ በተጨማሪም ምስክሮቹ ገዥው ፓርቲን የሚደግፉና የወጣት ሊግ አባል ሆነው ገዥው ፓርቲን የሚቃወም ግለሰብ ላይ የሰጡት ምስክርነት ገለልተኛ ነው ብሎ ለማመን ያስቸግራል ብሏል፡፡
ከዚህም ባሻገር ምስክሮቹ የገዥው ፓርቲ ደጋፊ ሆነው እያለ አቶ ማሙሸት አማረ በተደጋጋሚ ይደውልላቸው እና ይገናኙም እንደነበር የመሰከሩ ሲሆን አቶ ማሙሸት ቀንደኛ የገዥው ፓርቲ ተቃዋሚ ሆኖ እያለ ከመንግስት (ከገዥው ፓርቲ) ቀንደኛ ደጋፊዎች እንዲህ አይነት ግንኙነት ይኖረዋል ብሎ ለማመን እንደማይቻል አስረድቷል፡፡ በሌላ በኩል ከ4 አመት ጀምሮ እስከ 7 አመት አዲስ አበባ ውስጥ የኖሩት ምስክሮች ስለ ሰልፉ ባስረዱበት ወቅት ቤተ መንግስትን ጨምሮ ሰልፉ ያለፈባቸውን ቦታዎች አናውቃቸውም ማለታቸው ራሳቸውን ከመስቀለኛ ጥያቄ ለማዳን ያደረጉት እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ገልጾአል፡፡ በመሆኑም የምስክሮቹ ቃል ታማኒነት ስለሌለው አቶ ማሙሸት አማረ መከላከል ሳያስፈልገው በዛሬው ዕለት በነፃ እንዲለቀቅ ሲል ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡
አቶ ማሙሸት አማረ ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም በተካሄደው ሰልፍ ላይ ሁከትና ብጥብጥ ፈጥሯል በሚል ተከሶ የነበር ቢሆንም በወቅቱ ከምርጫ ቦርድ ጋር በነበረው ክርክር ሰልፉ ላይ አለመገኘቱን የሚያጋግጥ መረጃ በማምጣቱ በነፃ እንዲለቀቅ ተወስኖ ነበር፡፡ ነገር ግን ክሱ ወደማነሳሳት ተቀይሮ እስከዛሬ እስር ቤት እንዲቆይ ተደርጓል፡፡

wanted officials