Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, January 31, 2016

“ወታደሮቻችን ያሉት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፤ ትግላችንን ለመቀላቀል ካሁን በኋላ ለምትፈልጉ ወደ ሰሜን ብቻ መሄድ የለባችሁም” ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

Screen Shot 2016-01-31 at 4.01.56 PM

“የብሔር ጥያቄን የመለሰች፤ ከራሷ ጋር የታረቀች ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን”

– ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

(ዘ-ሐበሻ) የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ ባደረጉት ሕዝባዊ ስብሰባ በኢትዮጵያ በተከሰተው ረሃብ; በኦሮሞ ተማሪዎች አመጽ እና ትግሉ ስላለበት ሁኔታ እንዲሁም ስለተቃዋሚዎች ተናግረዋል::
በኢትዮጵያ የተከሰተው ረሃብ የስርዓቱ ችግር ነው ካሉ በኋላ እርሳቸው የሚመሩት ተቋም ከዚህ ቀደም የገመተው የተራቢዎች ቁጥር አሁን ተግባራዊ እየሆነ እንደሆነ እንዲሁም ይህ አስተዳደር ከቀጠለ ከዚህ ቀደም እንደገመቱት በ2050 ዓ.ም 50 ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚራብ ገልጸዋል::
በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ዙሪያም እንዲሁ የተናገሩት ፕሮፌሰሩ በኦሮሚያ ክልል ህፃናት እና ነብሰጡርን ሳይቀር እየገደለ ያለውን ስርዓት ሕዝቡ እየሞተ ያለው ወገኔ ነው ብሎ ማውገዝ አለበት ብለዋል:: በተለይም በአሁኑ ወቅት ከኦሮሞ ድርጅቶች ጋር በህብረት ለመታገል ንግግሮች መጀመራቸውንም አስታውቀዋል::
ስለተቃዋሚዎችም የተናገሩት ፕሮፌሰሩ “የተቃዋሚዎች የምኞት ፖለቲካ ነው የሚከተሉት” ሲሉ ተችተው የምር መታገል እንዳለባቸው አስምረውበታል::
ወቅታዊውን የአርበኞች ግንቦት 7 ሁኔታ በተመለከተም “ወታደሮቻችን ያሉት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው… ትግላችንን ለመቀላቀል ካሁን በኋላ ለምትፈልጉ ወደ ሰሜን ብቻ መሄድ የለባችሁም” ብለዋል::
ሙሉ ንግግራቸውን ይዘን እንመለሳለን::

“ዕድሜዬም ኃይማኖቴም አይፈቅድም ስንቅ መቀበሉ ይቀራል እንጅ አትነኩኝም” እስክንድር ነጋ!!

Eskinder Nega 23በትላንትናው ዕለት እስክንድርን ለመጠየቅና ስንቅ ለማቀበል የሄዱ ቤተሰቦቻችን እስክንድርን ማግኘት ሳይችሉ የቋጠሩትን ምግብ ይዘው መመለሳቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ምክንያቱ ደግሞ፣ እስክንድር ቤተሰብ ለማግኘት ከክፍሉ ሲወጣ የደረሰበት መብቱን የጣሰ ፍተሻ ነበር።
የትላንትናው ፍተሻ ባልተለመደ መልኩ ብልት አካባቢ ከፍተኛ መነካካትን ያካተተ እንደነበር ከውስጥ አዋቂዎች ለማወቅ ችያለሁ። እስክንድር ይህንን ብልት ላይ የሚደረግን ፍተሻ ” ዕድሜዬም፣ኃይማኖቴም ስለማይፈቅድ ስንቅ መቀበሉ ይቀራል እንጅ ( ብልቴን መንካት) አትችሉም” በሚል ከቤተሰብ ሳይገናኝና የገባለትን ምግብም ሳይቀበል መቅረቱን ለማወቅ ችያለሁ። ህምምምም!!
በእነሱው እስር ቤት፣በእነሱው ጥበቃ ሥር ያለን ግለሰብ ስንቅ ለመቀበል ሲወጣ በእንትኑ ቦንብ ያንጠለጠለ ይመስል እንደዚህ ማዋከቡ የሰዎቹን ፍርሃት ልክ ከጣራ በላይ መዋሉን ያሳያል።
“ጉድጓዱን አርቀህ አትቆፍር የሚገባበት አይታወቅምና!”
እኛም እንላለን እስክንድር ሆይ መብትህን አሳልፈህ አትስጥ፣በመብትህ አትደራደር…ሰባት ሞት የለምና!!

የጋምቤላው ግጭት ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል

12631426_1679241445680385_2889185539867169905_n
በቅርቡ የብሄር ብሄረሰብ ቀን የተከበረባትና የብሄሮች መቻቻል ኣንድነት እና ፍቅር ተምሳሌት ተደርጋ በወያኔ ኣገዛዝ የተንቆለጳጰሰችው ጋምቤላ በጎሳ ጦርነት እየተናጠች ነው ። አዲስ ስታንዳርድ የተባለው እንግሊዘኛ ድህረገጽ ባወጣው ሰበር ዜና መሰረት በጋምቤላ ክልል በተነሳው ግጭት ቀጥሎ በጋምቤላ ከተማ እስር ቤት ላይ በደረሰ ኣደጋ ቢያንስ ሰባት ሰዎች መሞታቸውን ዘግቧል።አስር ቤቱን ሰብረው ለመግባት የኑኤር ተወላጆች ባደረጉት ግጭት ሰባቱ ሰዎች መገደላቸው ታውቋል።
በቦታው የነበረውን የኣይን ምስክር ያነጋገረው ኣዲስ ስታንዳርድ እንደዘገበው የኑኤር አና ኣኝዋክ ጎሳን ግጭት ተከትሎ በጋምቤላ ከተማ ኣራት ኪሎ ተብሎ በሚጠሯው የጋምቤላ ማረሚያ ቤት ላይ የታጠቁ የኑኤር ተወላጆች ከባድ ጥቃት ኣድርሰዋል።በግጭቱ ተጎድቶ ለሕክምና የመጣ ሰው ዋቢ ያደረገ ዘገባው ጋምቤላ መንግስት ኣልባ ሆናለች ብሏል፥ኣከባቢው ላይ የሰፈሩ የወያኔ ፖሊሶች አና ወታደሮች የጋምቤላ ከተማ ፖሊሶችን ትጥቅ ኣስፈትተዋቸዋል።
በኣከባቢው ግጭት የተነሳው በሁለቱ ኦሳዎች ኣባላት ግለሰቦች መካከል በመሬት ቁርሾ ኣለመግባባት ተከትሎ የተነሳውን ተኩስ እና ከቁትትር ውጪ የወጣውን ግጭት ኣስታኮ የክልሉ ታጣቂዎች የኑኤር ተወላጆችን ኣፍሰው ማሰር ከጀመሩ በኋላ መሆኑ ታውቋል። በክልሉ ኣሁንም ግጭቱ የቀጠለ ሲሆን በከተማው ከፍተኛ ውጥረት ኣይሏል።
ምኒሊክ ሳልሳዊ

የሐዋሳውን የመሬት መንቀጥቀጥ ሽሽት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ በመኪና አደጋ የሞቱት ተማሪዎች ቀብር ዛሬ ይፈጸማል

hawasa
ከዳዊት ሰለሞን
በሐዋሳ በተደጋጋሚ የተከሰተውን የመሬት መንቀጥቀጥ በመሸሽ ወደ አዲስ አበባ በማምራት ላይ የነበሩ የሐዋሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መቂ አዋሽ ወንዝ ድልድይ ጋር እንደደረሱ የተሳፈሩባት ሚኒባስ ከከባድ መኪና ጋር በመላተሟ ህይወታቸው ማለፉ አይዘነጋም ።
በአደጋው ህይወታቸውን ያጡት የአላማጣ ልጆችና ከ25-18 ባለ የእድሜ ክልል ውስጥ ይገኙ የነበሩ የሁለተኛ ዓመት የኢንጂነሪንግ ተማሪዎች ናቸው ።አገራችን አራት ኢንጅነሮችን በአንድ ቅፅበት አጥታለች ማለት ነው ።
1- አሸናፊ ተካ – እድሜ 25 – የሃይድሮሊክ ኢንጂነሪንግ ተማሪ
2 – አበበ ሞረሳ – እድሜ 23 የኬሚካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ
3 – ኢዮብ ህሉፍ – እድሜ 20 የኬሚካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ
4 – ሀየሎም በርሄ እድሜ 18 የመካኒካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ።
ዛሬ በአለማጣ ከተማ ስርዓተ ቀብራቸው የሚፈፀምላቸውን ተማሪዎች ነፍስ አምላክ ያሳርፍ፣ ለቤተሰቦቻቸው ፣ለወዳጆቻቸውና ለሐዋሳ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ መፅናናትን ይስጥልን ።

ድርቁ አስጨናቂና አሳሳቢ ሆኗል ተባለ – አዲስ አድማስ

በድርቁ አካባቢዎች 350ሺ ተጨማሪ ህፃናት ይወለዳሉ
  • የነፍሰ ጡር እናቶች ቁጥር እየጨመረ ነው
  •  የእርዳታ እህል በፍጥነት እንዲጓጓዝ ተጠየቀ
በድርቅ በተጐዱ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በሚቀጥሉት 6 ወራት ውስጥ 350ሺህ ተጨማሪ ህፃናት እንደሚወለዱ የተባበሩት መንግስታት ያስታወቀ ሲሆን ለድርቁ የሚደረገው አለማቀፍ ድጋፍ የተቀዛቀዘ መሆኑ ችግሩን አስጨናቂና በእጅጉ አሳሳቢ አድርጐታል ተብሏል፡፡
አለማቀፉ የህፃናት አድን ድርጅት በበኩሉ፤ በአሁኑ ወቅት ከሶሪያ ቀጥሎ አሠቃቂ የሰብአዊ ቀውስ ያንዣበበው በኢትዮጵያ መሆኑን ጠቁሞ፤ 4መቶ ሺህ ህፃናት የአልሚ ምግብ በእጅጉ እንደሚያስፈልጋቸው ገልጿል፡፡
ድርቁ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ባለሙያዎቹን በመላክ ተዘዋውረው እንዲጎበኙ ማድረጉን የጠቆመው የህፃናት አድን ድርጅቱ፤ በርካታ እናቶች ነፍሰ ጡር መሆናቸው አሳሳቢ እንደሆነ ገልጿል፡፡ ለእናቶች እንክብካቤ ማድረግ አስቸጋሪ በሆነበት እንዲሁም እናቶች አስፈላጊውን ንጥረ ምግብ ማግኘት ባልቻሉበት ሁኔታ የነፍሰ ጡር ሴቶች ቁጥር መጨመር ችግሩን አስጨናቂ ያደርገዋል ተብሏል፡፡ የሚወለዱት ህፃናት እጣ ፈንታም አሳሳቢ የህፃናት አድን ድርጅቱና የተባበሩት መንግስታት ጠቁመዋል፡፡
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት ድርቁን ለመቋቋም እያደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ ከ10.5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ለማውጣት እንደሚገደድ የአለም የምግብ ፕሮግራም ከትናንት በስቲያ ያስታወቀ ሲሆን የገንዘብ ድጋፉም እስከ ሚያዚያ ወር ድረስ ተሰባስቦ ለተረጅዎች ድጋፍ መዋል እንዳለበት ገልጿል፡፡
በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች የድርቁ ሁኔታ በ1977 ዓ.ም ከተከሰተውና የ1 ሚሊዮን ገደማ ዜጐችን ህይወት ከቀጠፈው የድርቅ ክስተት የባሰ መሆኑን የጠቆመው የአለም የምግብ ፕሮግራም፤ 10.5 ቢሊዮን ብሩን በመጪው ወር ከለጋሾች እንደሚያሰባስብም ገልጿል፡፡
በአጠቃላይ ለእርዳታው ያስፈልጋል ተብሎ ከተገመተው 1.4 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ በአሁኑ ወቅት 37 በመቶ ያህሉ መገኘቱን የተባበሩት መንግስታት የእርዳታ ማስተባበሪያ ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡
የብሔራዊ የአደጋና ስጋት ቅነሳ ስራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ፤ መንግስት ለተጐጂዎች በቂ እርዳታና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልፆ እስካሁን ከተለያዩ አገራትና የረድኤት ተቋማት 431 ሚ. ዶላር ድጋፍ ቃል መገባቱን አስታውቋል።
የመንገድ ችግርና የመጋዘን እጥረት እርዳታ በማከፋፈል ሂደቱ የሚገጥሙ እንቅፋቶች እንደሆኑም ኮሚሽኑ ጨምሮ ገልጿል፡፡
የተባበሩት መንግስታት የእርዳታ ማስተባበሪያ ኤጀንሲ በበኩሉ በእርዳታ አሰጣጡ ላይ ዘይት፣ ስንዴና የማባያ የምግብ ግብአቶች በአንድነት ለተረጂዎች እየቀረቡ አለመሆኑ እርዳታ ፈላጊዎች ለእንግልት እየዳረገ መሆኑን ጠቅሶ፤ የምግብ ግብአቶች በአንድነት እንዲቀርቡ ጠይቋል፡፡
እስከ ሚያዚያ 2008 የሚበቃ እርዳታ መገኘቱን የጠቆመው ኤጀንሲው፤ እርዳታውን ከወደብ የማጓጓዝ ሥራ በፍጥነት መከናወን እንዳለበት አሳስቧል፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአጭር የሞባይል የጽሑፍ መልዕክት ስኬታማ የሆነ እርዳታ እያሰባሰበ መሆኑን  አስታውቋል፡፡ የማህበሩ የኮሚኒኬሽንና የሃብት ማሰባሰብ መምሪያ ሃላፊ አቶ ደግሰው አማኑ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ በአጭር ጽሑፍ መልዕክቱ እርዳታ የሚያዋጣው የህብረተሰብ ቁጥር በየእለቱ እየጨመረ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀን እስከ 10ሺህ ሰው ከ5 ብር 50 ብር የሚደርስ የገንዘብ እርዳታ እየሰጠ እንደሆነ ተረጋግጧል ብለዋል፡፡

Thursday, January 28, 2016

ፍ/ቤቱ በአቶ ዮናታን ተስፋየ ላይ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ

ፍ/ቤቱ በአቶ ዮናታን ተስፋየ ላይ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ
*‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› ዮናታን ተስፋየ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለ2ኛ ጊዜ የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል፡፡
ዛሬ ጥር 17/2008 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበው አቶ ዮናታን ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም በሚል የጠየቀበትን ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ ለየካቲት 15/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ አቶ ዮናታን ተስፋየ የዋስትና መብቱ እንዲከበርለት ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡
ፖሊስ በአቶ ዮናታን ላይ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ሲጠይቅ ‹‹የቴክኒክ መረጃዎችን መሰብሰብ ይቀረናል፤ ያልተያዙ ግብረ አበሮችንም አሉ›› የሚል ምክንያት ማቅረቡን የተጠርጣሪ ጠበቃ ገልጸዋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ በጠበቃ እና በቤተሰቦቹ እንዳይጎበኝ እንደተከለከለና ከታሰረበት ክፍል መታፈን የተነሳ የጤና እከል ቢገጥመውም ህክምና እንዳላገኘ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን አድምጦ በጠበቃውም ሆነ በቤተሰቦቹ እንዲጎበኝ እንዲፈቀድለትና ህክምናም እንዲያገኝ ትዕዛዝ መስጠቱን ከጠበቃው ለማወቅ ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ከችሎት ሲወጣ በስፍራው ለነበሩት ቤተሰቦቹና ወዳጆቹ ያለውን ፍቅር ገልጾ ‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› በማለት ጮክ ብሎ ሲናገር ተደምጧል፡፡

(የአቡነ መልኬጼዲቅና የኦርጋኑ ጉዳይ) ባልበላውም ጭሬ ደፋዋለሁ አለች ዶሮ !! | ጥቂት ጥያቄ መልስኛ ስለ ኦርጋን

(የአቡነ መልኬጼዲቅና የኦርጋኑ ጉዳይ) ባልበላውም ጭሬ ደፋዋለሁ አለች ዶሮ !! | ጥቂት ጥያቄ መልስኛ ስለ ኦርጋን


Abune Melekestedik Organ
ከመኳንንት ታዬ
ሰው ማንነቱን በራሱ ማስተዋል ሲቆጥበው ያለነጋሪ እንደሚያተርፍ አውን ነው።ማትረፉ በራሱ የንግዱ መልካም መሆንን አያመላክትም።አንዳንዴ ተፈላጊው ነገር ገበያ ላይ እንብዛም ባለመኖሩ ረባም አረባም የሚፈለገው ነገር እስካለ ብቻ ገዢም የሚገዛበት ሻጭም አንዲሸጥ እድል ይሰጠዋል።

ይህ የማትረፉ አለም ውጣ ውረድ ነው።ሰውም በማንነቱ እንዲሁ የሚሆንበት አጋጣሚ አለ።ትልቅ የሚባል ፤መልካም የሚባል ሃይማኖቱን አክባሪ የሚባል ፤ ብቻ እንደሁነቱ አሳሳቢነት ለስፍር የሚሞላ ማንነት አለው የምንለው ሰው ሲጠፋ ፤ይሻላል የሚባል ከማይሻሉት የተሻለ ይመረጣል።
ይህ ሁሉ ምርጫ ለሚሰጥ ወይም ላለው ነገር ነው ።ሃይማኖት ማለት ግን አንድ እና አንድ ነው። መሆን አለመሆን።ከዚህ ያለፈ ስሌትም ባለቤትነትም አይኖረውም።ብዙዎች ለስህተታቸው ማስታገሻ የሚያደርጉት የነሱን አላዋቂነት ሳይሆን ድሮ እያወቁ ቆይተው ዛሬ መርሳታቸውን ባለማስታውስ ነው ።
ይህቺን ደረሰኝ የምታክል ፅሁፍ እንድከትባት ያስቻለኝ በቅርቡ የተለየ የመዝሙር መሳሪያን በተመለከተ በስደት እገኛለሁ ከሚሉ አንድ አባት የተሰነዘረው ሃሰብ ነው።በርግጥ ከላይ ለማለት እንደሞከርኩት ሰው ችግር የሚገጥመው ከሃገሩ ሲሰደድ ሳይሆን ከማንነቱ ሲሰደድ ነው። ለዚህም እንደማስረጃ ከምንይዛቸው ነገሮች እንዲህ እንደ አሁኔው አይነት ነገሮችን ስናይ ለግምትም ለማለትም እንቸገራለን።አውነት ነው። ላያስደነግጠንም ላያሳስበንም ይችላል ። እንቅስቃሴውም አሁን አደለም ።አሁን ንግግር የሆነበት ምክንያት ሲደመር ስለሆነ ነው።ግን እኮ ኦርጋን ሌሎች ይጠቀማሉ ።ስለዚህ እኛም መጠቀም አለበን ነው የሚሉን አቡነ መልከፀዲቅ።
ደግ እሳቸው ተቀብለውታል ።ለማስረጃውም ሌሎችን ጠቅሰዋል።እንግዲህ ልፋ ያለው ….. ከሆነ ምን ይደረጋል። ግን እኮ ሌሎች እኛ ልንበላ ጨርሶ የማንችለውን አህያ እና ፈረስ እየበሉ ክርስቶስን የሚያመልኩ አሉ።ለዚህም ደግሞ እንደማስረጃ ሮሜ ም14 ከቁጥር፩-፬ ድረስ እንዲህ ተብሎአል።በእምነት የደከመውን ተቀበሉት በአሳቡም ላይ አትፍረዱ።
ሁሉን ይበላ ዘንድ እንደ ተፈቀደለት የሚያምን አለ፤ ደካማው ግን አትክልት ይበላል ይላል…”ይህ እንግዲህ በመፅሃፍ የተፈቀደ እና ያልተፈቀደ ፤የሚያፅይፍ የሚበላ እና የማያፀይፍ የሚበላ አለ።በመፅሃፍ እንደተናገረ። በዚህ አውነት ሌሎች ሃገር የሚገኙ ኦርቶዶክሳዊያን ከላይ የተጠቀሱትን ፈረስ ወይም ውሻ ወይም ለእኛ ለኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሃዶ አማኞች ለመብልም ለባህሪያችንም ያልተፈቀደ ነገር የሌላ ሃገር ኦርቶዶክሶች ስለ በሉ ይበላሉ ወይ ?አሁን ባሉበት ሁኔታ አብነት መሆን ከሆነ እንግዲህ ይብሉና ይኸው እኔ በላሁ ብለው ያሳዩንና ስላኦርጋኑ እናስብበት ።አለዚያ ብዙ የሚሰራ ስራ እያለ በኑፋቄ ስራ ላይ ተሰማርቶ”ባልበላውም ጭሬ ደፋዋለሁ እንዳለችው ዶሮ “የሚሆንበዎ ይመስለኛል ።
ለዚህም ነው ከሃገር ብቻ ሳይሆን ከማንነታችንም እየተሰደድን ይመስላል ለማለት ያስደፈረኝ ።ወደ መፅሃፍ ቅዱሳዊው መልስ ስንጓዝ በስህተትም በኦርጋን አመስግኑ የሚል አላየንም። ስለዚህ ከተሰበከልን ወንጌል ውጭ የሚሰብከንን መላአክትም ቢሆነ እንዳንቀበል መፅሃፍ ያዛልና አንቀበልም።
ይቆየን

የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከካርታ ስራ ድርጅት ወጥቶ በደህንነት መስሪያ ቤት እንዲሰራ መደረጉ መሬት እንደፈለጉ ለመስጠት እንዲመች ነው ተባለ



የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከካርታ ስራ ድርጅት ወጥቶ በደህንነት መስሪያ ቤት እንዲሰራ መደረጉ መሬት እንደፈለጉ ለመስጠት እንዲመች ነው ተባለ
በመረጃና ደህንነት ኤጀንሲ ( ኢንሳ) ውስጥ ተቀጥሮ የሚሰራ አንድ ከፍተኛ ባለሙያ ለኢሳት እንደገለጸው፣ የኢትዮጵያን የመሬት መረጃ የሚሰበስብ የኢትዮጵያ ካርታ ስራ ኤጀንሲ የተባለ መስሪያ ቤት ቢኖርም፣ መንግስት ፎቶ የማንሳቱ ስራ በኢንሳ ስራ ማድረጉ የተለያዩ አላማዎችን ለማስፈጸም ነው ይላል። የመረጃ ደህንነት ኤጀንሲ በአንድ ብሄር የተያዘ፣ ከመከላከያው ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው እንዲሁም ለወያኔ ድርጀቶችና ደጋፊዎች መሬት በመስጠት ፣ የወያኔን የፖለቲካ ኢኮኖሚ ደግፈው እንዲይዙ ለማድረግ ነው ይላል። እስካሁን 46 የፎቶ መቆጣጠሪያ ምልክቶች ተስርተው ያለቁ ሲሆን፣ የአየር ላይ ፎቶ የማንሳቱ ስራ እየተሰራ እያለ ለ2 ሳምንታት በአየር ጸባይ ምክንያት እንዲሁም በአካባቢው እየተነሳ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞ የተነሳ የአየር መቆጣጠሪያ ምልክት ለማቆም ባለመቻሉ እንዲቆም ከተደረገ በሁዋላ፣ ፎቶ የማንሳቱ ስራ እንደገና ተጀምሯል። በመጀመሪያው ዙር የሚካሄደው የፎቶ ማንሳት ስራ ከመተማ እስከ ቋራ ያለውን ወደ 365 ኪሜ እርዝመት ያለው መሬት የሚሸፍን ሲሆን ፣ በሂደትም በቤንሻንጉል ክልል አካባቢ ያለውን ፎቶ የማንሳቱ ስራ ይቀጥላል። አሁን አንገብጋቢው ነገር ይላል ባለሙያው፣ በጎንደርና በሱዳን እንዲሁም በጎንደርና በምእራብ ትግራይ የሚሰሩ የአየር መቆጣጠሪያ ምልክቶች እንዳይሰሩ የአካባቢው ህዝብ በንቃት መጠበቅ እንዳለበት ባለሙያው ገልጿል

17 Children Killed by Authorities in Ethiopia Land Protests

Burial of Nasrudin Mohammed, a protester killed in December 2015. Photograph by Gadaa.com.
Burial of Nasrudin Mohammed, a protester killed in December 2015. Photograph by Gadaa.com.
(Global Voices) — Ethiopian authorities have killed at least 17 children and injured many more involved in peaceful land rights protests since December 2015.
Demonstrations over a plan to expand the capital into the ethnic region of Oromia began in Ethiopia in late November. Since then, there have been 140 confirmed deaths of protesters at the hands of government authorities. Of the 17 minors killed by authorities, most were between the ages of 12 and 17 years old. Citizen media reports also show that many more school children have been injured in the protest movement.
The protesters are speaking out against the so-called “Master Plan” to expand the capital city, Addis Ababa, into Oromia, fearing that the proposed development will result in direct persecution of the Oromo ethnic group, including mass evictions of Oromo farmers from their land. Oromo people, who represent the largest ethnic group in Ethiopia, have experienced systematic marginalization and persecution over the last quarter century. Some estimates put the number of Oromo political prisoners in Ethiopia at 20,000 as of March 2014. The country’s ruling elite, of the EPRDF party, are mostly from the Tigray (only 6% of Ethiopia’s 90 million population ) region, which is located in the northern part of the country.
In parallel with efforts of global organizations such as Human Rights Watch, local activists have worked to document and preserve evidence of these killings since early December. Last week, Ethiopian media scholar Endalk Chala and Oromo activist Abiy Atomssa published a map of confirmed deaths based on a crowdsourced data set comprised of reports from citizens, activists, social media, local media networks and VOA’s Amharic service.
Ethiopia: Deaths of Minors in Oromo Protests, December 2015 : minors killed december 2015

NameDescriptionWhereWhenRemarks
Gutu Abara Dheressa12th Grade Student at Chaliya High SchoolGuliso, West Walaga)12/2/2015
Dejene Serbessa10th Grade Student at Bantu Secondary SchoolTole, South West Shawa)12/3/2015
Miftah Juneydi BushraHigh School StudentFurda Town, Bedeno, East Hararge12/5/2015
Murad [Murata] Abdi Ibrahim9th Grade Student at Bate High SchoolIn front of Haromaya University12/7/2015Funeral on 8 Dec 15 in Kombolcha
Bekele Seifu11th Grade StudentInchini, West Shawa12/7/2015Killed on spot
Bekele Seboka Hunde12th Grade Student at Inchini Preparatory SchoolInchini, West Shawa12/7/2015Shot & wounded. Died before reaching Paulos Hospital
Banti DhugumaBurqa Wanjo Secondary schoolLalo Asabi district, West Walaga12/10/2015
Alazar Kelbessa [Benti]StudentInango, West Walaga12/10/2015
Lucha Gamachu9th grade student at Burqa Wanjo Secondary SchoolInango, West Walaga12/10/2015https://www.facebook.com/Jawarmd/videos/10102047226079323/?theater
Gudata Bayissa Gobena9th grade studentBabichi, West Shawa12/10/2015
Dereje Gadissa Taye9th grade studentBabichi, West Shawa12/10/2015
Fikadu Girma9th grade studentGedo, West Shawa12/10/2015
Lamessa Fayera12 years old studentAmbo, West Shawa12/12/2015
Ulfata Chimdi4th grade student. Age 12Ambo, West Shawa12/12/2015
Tadasse Dhaba Jobir8th grade student at Gixire Elementary schoolAbuna, Gindabarat, West Shawa12/14/2015wounded on 14 Dec 15. Funeral on 16 Dec 15
Name not yet identifiedYoung ageAwaday, East Hararge12/15/2015
Name not yet identifiedYoung ageAwaday, East Hararge12/15/2015
Damee Dabali10th grade studentMaqa-Najjo, West Walaga12/15/2015soldiers would not allow the public remove the body for several hours as they kept firing
Barihun Shibiru8th grade studentEjaji, West Shawa12/16/2015Arrested and executed. Funeral date 17 Dec 15
Eshetu FedessaSon of Sirne GudataChanka, Qellam, West Wallaga12/17/2015http://amharic.voanews.com/audio/3102692.html
Eighth grader Barihun Shibiru of West Shawa was among a handful of minors who were arrested and executed once in official custody. Shibiru’s funeral was held on December 17.
Citizen videos have also helped document and confirm deaths of minors, including a video that shows students crowding around the body of Lucha Gamachu, a 9th grader at Burqa Wanjo Secondary School.
- See more at: http://www.zehabesha.com/17-children-killed-by-authorities-in-ethiopia-land-protests/#sthash.4LYY9nZ9.dpuf

Wednesday, January 27, 2016

በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች ግድግዳዎች ላይ የተቃውሞ ጽሑፎች ተጽፈው አደሩ




(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች በሚገኙ ግድግድዎች ላይ በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት የሚቃወሙና ጥያቄም የሚጠይቁ መፈክሮች ተጽፈው አደሩ:: በተለይ መንግስት ያሰራቸውን የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ፍርድ የሚቃወም; በሃገሪቱ በተቃዋሚዎች ላይ የሚሰጡ ፖለቲካዊ ፍርዶችን የሚቃወሙ; በኦሮሞ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ግድያ የሚያወግዙና ሌሎችም መፈክሮች በትላልቁ በግድግዳዎች ላይ ተጽፈው አድረዋል::
ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ተቃውሟቸውን በስርዓቱ ላይ ቢያሰሙም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የሕዝቡን ጥያቄ ወደ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚል አሁንም በርካታ ጋዜጠኞችን; የሃይማኖት መሪዎችን; የፖለቲካ ሰዎችን አስሮ በማሰቃየት እንዲሁም በመግደልም ላይ ይገኛል::
በአዲስ አበባ ግድግዳዎች ላይ ተጽፈው ያደሩ ተቃውሞዎችን በፎቶ ይመልከቱ::
addis ababa 3addis ababaaddis ababa1addis ababa2

ከሰይፉ ፋንታሁን እና ሚኪያስ መሐመድ ቃለምልልስ በስተጀርባ – (ከሰራተኞቹ አንዱ)




Mikiyas
አርቲስት ሚኪያስ መሐመድ የተለያዩ ሰዎችን ‹‹ጎማ እናስመጣ›› እንዲሁም በአንድ ወቅት ንሮ የነበረውን የሲሚንቶ ገበያ ሰበብ በማድረግ ‹‹የማውቃቸው ሰዎች አሉና ሲሚንቶ አብረን እንነግድ›› በማለት ነበር እንቅስቃሴውን የጀመረው፡፡
ሚኪ ወደዚህ ስራ ሲገባ በቀላሉ የሚያውቃቸውንና ገንዘብ አላቸው ብሎ የሚተማመንባቸውን ሰዎች ማጥመድ ጀመረ፡፡ በዚህ ወጥመድ ውስጥ የተወሰኑ ባለሀብቶች ገብተውለት 8 ሚሊዮን ብር ገደማ ሲያገኝ የተጠቀሰውን ያህል መጠን ያለው ቼክም ፅፎ ሰጣቸው፡፡ ቼኩ በቂ ስንቅ(ገንዘብ) የሌለው መሆኑን ባለሀብቶቹ ሲረዱ እንደተጭበረበሩ የገባቸው ሲሆን፤ ከእነዚህ ሰዎች አንዱ(2 ሚሊዮን ብር የሰጡት) ጉዳያቸውን ይዘው ወደቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አቀኑ፡፡ የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስም አቶ ሚኪያስ መሐመድን በጷግሜ ወር በቁጥጥር ስር አዋለው፡፡
በፖሊስ ጣቢያው ከሳሽና ተከሳሽ ፊት ለፊት ሲገናኙ ተከሳሽ ሚኪ ስቅስቅ ብሎ እያለቀሰ የከሳሽ እግር ስር ወድቆ ተማፀነ፡፡ ‹‹እንደራደር›› ሲልም ጥያቄ አቀረበ፡፡ በዚህ መሰረት ግማሽ ክፍያ ወዲያውኑ ለመስጠትና ቀሪውን ደግሞ በ15 ቀናት ውስጥ ለመክፈል ጊዜ እንዲሰጠው መደራደሪያ አመጣ፡፡ በዚህ መሐል ነው እንግዲህ ምስኪኑ ራስታ ዘፋኝ ህይወቱን ሙሉ ያጠራቀመውን ገንዘብ አንስቶ ለሚኪ የሰጠው፡፡ ሚኪም ከታደለ ሮባ የወሰደውን ገንዘብ ከተከሰሰበት 1.7 የሚሊዮን ብር ዕዳ ግማሹን ሊከፍል ቻለ፡፡
ይህ ሁሉ ሁኔታ ሲሆን ማለትም ሚኪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሲውል ዛሬ እያስተባበለ ያለው ሰይፉ ፋንታሁን ሊያገባ ጥቂት ቀናት ቀርተውት ነበር፡፡ ሚዜውም ነበር፡፡ ሙሽራውና ሚዜዎች ስቲም ሊገቡ ቀጠሮ በነበራቸው ቀን ሚኪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ስለነበር ሳይገኝ ቀርቷል፡፡ ከእስር ከተፈታ በኋላ ሰርጉ ሲከናወን ይህንን ሚስጥር የሚያውቁት ሚኪና ታደለ ብቻ ነበሩ፡፡ እናም ውሾን ያነሳ… ተባባለው ተማማሉ፡፡
ከሰርጉ ስነስርዓት በኋላ የሚኪ ስልክ ድንገት ዝግ መሆኑ ግን ግራ የሚያጋባ ሆነ፡፡ በዚያ ላይ አሜሪካ የመግባቱ ጉዳይም መወራት ጀመረ፡፡ እሱ ግን በቫይበር ከሚደወሉለት ስልኮች ውስጥ የአንድ ሰውን ጥሪ ብቻ ያነሳ ነበር፡፡ የሰራዊት ፍቅሬን!!
በዚህ ወቅት ከሚኪያስ መሐመድ ቼክ የተሰጣቸው ሰዎች በሙሉ ወደባንክ መጉረፍ ጀመሩ፡፡ ቼኩን አስመትተውም አርቲስቱ የሚመጣበትን ቀን መጠባበቅና መፀለይ ሆነ ስራቸው፡፡ ይሁንና በመሀል ሽምግልና ተብሎ እነዚህ ቼኮች በሙሉ ተሰበሰቡ፡፡
(በዚህ ወቅት አማን(ጀርመኑ) ለተባለ ወጣት ከሚኪ የተፃፈለትን የ350ሺህ ብር ቼክ ልብ ያለው ሰው አልነበረም፡፡ ይህ ወጣትም ቼኩን አስመትቶ ጉዳዩን አቃቤ ህግ ጋር አድርሶታል፡፡)
Mikiyas Mohamed
ከሽምግልናው ጎን ለጎን ድምፃዊ ታደለ ሮባ ‹‹ይህን ያህል አመት የሰራሁበትን ገንዘብ ዘረፈኝ፤ ጉድ አደረገኝ›› እያለ የሚኪ እናት ቤት ይመላለስ ነበር፡፡ እናትየውም ‹‹አይዞህ ቤቴን ሸጬም ቢሆን እከፍላችኋለሁ እንጂ ልጄን ከሳችሁ አታሳስሩብኝ›› ይሉ ጀመር፡፡
የእናትየው ሀዘንና ቼክ የተጭበረበሩ ሰዎች ለቅሶ ያሳዘነው ዮናስ ቬጋስ ‹ጉዳዩን ለኔ ተውት›› ብሎ እንቅስቃሴ ጀመረ፡፡ እንቅስቃሴው ሚኪን ከአሜሪካ አስመጥቶ የእናቱን ቤት ሸጦም ቢሆን ቼክ ለተሰጣቸው ሰዎች ገንዘባቸው እንዲመለስላቸው የማድረግ ነው፡፡
በመሆኑም ዮናስ ቬጋስ ወደአሜሪካ አቀናና ከሚኪ ጋር ተገናኘ፡፡ ከቀናት በኋላም ታደለ ሮባ ተከተለው፡፡
የሚገርመው ‹‹በህይወት ዘመኑ የሰራበትን ገንዘብ የበላው›› እና ስልኩን ዘግቶ የጠፋበት ሚኪያስ መሐመድ በአሜሪካ ታደለ ሮባን አየር ማረፊያ ድረስ ሄዶ በመቀበል ሰርፕራይዝ አድርጎታል፡፡
በቀጣይነት ድርድሮችና ውይይቶች መደረግ ጀመሩ፡፡ በአደራና በሽምግልና ቼኮቹ የተቀመጡት ሰራዊት ፍቅሬ ጋር በመሆኑ ሚኪ በቀጥታ ለሰራዊት በመደወል ሁኔታውን አረጋገጠ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደኢትዮጵያ ተመልሶ አጭበርብሮበታል የተባለባቸውን ቼኮች ለመክፈል ተስማማ፡፡ የሚመለስበት ቀንም ተቆረጠ፡፡ ነገር ግን በዚህ መሀል አንድ ችግር ተፈጠረ፡፡ 350 ሺህ ብር የተበላው ወጣቱ አማን(ጀርመኑ) ‹‹ክሴን አላነሳም፤ በክሱ እቀጥልበታለሁ›› ሲል በአቋሙ ጸና፡፡ ሚኪያስም ‹‹እንደዚህ ከሆነማ አልመለስም በቃ!!›› ሲል ሀሳቡን የመቀየር ነገር አመጣ፡፡ አማንን(ጀርመኑን) የሚያውቁት ሰዎች በሙሉ ክሱን እንዲያቋርጥ ቢወተውቱትም አማን ግን በእንቢታው ፀና፡፡ (ይህኛውን ታሪክ በቀጣይ እንመለስበታለን)
የአማን ነገር እንደማይሆን ሲታወቅ ‹‹ያበጠው ይፈንዳ›› በሚል ይመስላል ሚኪያስ መሀመድና ታደለ ሮባ ከሎስ አንጀለስ በአንድ አውሮፕላን ተሳፍረው ቅዳሜ ጠዋት አዲስ አበባ ገቡ፡፡
አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ ሚኪያስ መሀመድ ለሽማግሌዎቹ አንድ ተማፅኖ አቅርቧል፡፡ ይህም ገንዘብ እንዳላጭበረበረና አሜሪካ የሄደው ለመዝናናት እንደሆነ በሚዲያዎች የሀሰት ዘገባ እንዲሰራለት ነው፡፡ ይህን የሀሰት ዘገባ ሰይፉ ፋንታሁን ብቻ ‹‹እሺ›› ብሎ ሲቀበል ሌሎች ለሙያቸው ያደሩ ጋዜጠኞች አንሰራም ብለዋል፡፡
እናም ዘሃበሻ ቀደም ብላ እንደጠቀሰችውም ሚኪያስ መሀመድ ቅዳሜ ምሽት ሰይፉ ሬዲዮ ላይ ቀርቦ የውሸት መአቱን የደረደረው ለዚህ ነው፡፡ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ጉዳዩን እያወቅን ዝም ብለን የቆየነውን እኛን ሰራተኞቹን መወንጀል ለምን አስፈለገው? እንላለን፡፡

wanted officials