Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, May 31, 2016

በስደት ያለው ሕጋዊው ሲኖዶስ 43ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቆ የአቋም መግለጫ አወጣ (ይዘነዋል)

43ኛው አጠቃላይ የህጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ
«ነገር ግን መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል።» ዕብ 13፥16 ሕጋዊው
 13245281_870480446413278_5481382366184526174_n
የኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከሐዋርያት ተያይዞ የመጣውን በዓመት ሁለት ጊዜ የሚያካሂደውን የርክበ ካህናት የሆነውን ጉባኤ በዚሁ ዓመትም በሲያትል ክብረ ቅዱሳን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተጋናጅነት ከግንቦት 17-19/2008 ዓ/ም ተካሂዷል። ጉባኤው በቤተክርስቲያናችንና በሀገራቸን ያለውን የወቅቱን መንፈሳዊና ማህበራዊ ችግሮች እና ሁኔታዎች የዳስሳና የመርመረ ጉባኤ ነበር ። ጉባኤው ከተጀመረበት እለት ጀምሮ መላው የጉባኤው አባላት ጠዋትና ማታ በጸሎት በመትጋት ፈቃደ እግዚኣብሔርን ጠይቆ በታላቅ መንፈሳዊነትና በትህትና ስሜት አካሂዷል ።

ሲውዲናዊቷ የኢትዮጵያውያን መብት ተሟጋች ሜሎዲ ሰንድበርግ (በማህሌት ፋንታሁን) Melody the Swedish Human right Activist for Ethiopia

በማህሌት ፋንታሁን
የመጀመሪያ ዲግሪዋን ሳይኮሎጂ ነው ያጠናችው። ከዛ በኋላም የህክምና ሳይንስ በተለይም የአእምሮ ህክምናን ተምራለች። በሙያዋም የአእምሮ ህሙማንን በማከም ታገለግላለች። በአለም ላይ በእስር ለሚገኙ ዘጋቢዎች እና ፎቶግራፈሮችን በገንዘብ ለመደገፍ የተቋቋመው ቃሊቲ ፋውንዴሽን የቦርድ አባል ናት። የመሳል፣ ፎቶግራፍ የማንሳት እና የመፃፍ ድንቅ ተሰጥኦ አላት -ስዊድናዊቷ ሜሎዲ ሰንድበርግ (Melody Sundberg)። ሜሎዲ የ27 አመት ወጣት እና ባለትዳርም ናት።
Melody Sundberg, Founder of Untold Stories
ስለ ሜሎዲ መጀመሪያ ያወቅኩት እስር ቤት ሆኜ ነው። የኔን እና ሌሎች አብረውኝ የታሰሩ ጓደኞቼን እንደሳለችን (sketch እንዳደረገች) እና ስእሎቹም በማህበራዊ ሚዲያ በሰፊው እየተሰራጩ መሆናቸውን ከቤተሰቦቼ ሰማሁ። በወቅቱ የተሰማኝን ስሜት በቃላት ማስቀመጥ ይከብደኛል። የህሊና እስረኛን ከሚጠቅሙነገሮች አንዱ አለመረሳት/ መታወስ ነው። እኛም እንዳንረሳ በየጊዜው በምትለቀው ፅሁፎቿ እና ስእሎቿ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጋለች። ከእስር ከወጣሁ በኋላ ከሜሎዲ ጋር በኢንቦክስ ስናወራ ህልም ህልም ነው የመሰለኝ። ከገፀ-ባህሪ ጋር የማወራ አይነት ነገር። እርግጠኛ ነኝ እየጮኸችላቸው ያሉ አሁን በእስር ያሉ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች፣ ፖለቲከኞች እንዲሁም የህሊና እስረኞች ተፈተው ከሜሎዲ ጋር የሚያወሩበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም።
እኛ ከተፈታን በኋላም ስራዋን ቀጥላለች ሜሎዲ። Untold Stories [http://www.untoldstoriesonline.com] በሚል ድረ ገፅ እና የፌስቡክ ፔጅ ተነግሮ የማያልቀውን በኢትዮጵያውያን ላይ በገዛ መንግስታቸው የደረሰባቸውን/እየደረሰባቸው ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት እና በደል ለአለም እያሰማች ነው። ያልተነገሩ እና ያልተሰሙ ታሪኮችን ቋንቋና ባህል ሳይገድባት መረጃዎችን አድና ማግኘቷ በጣም ይገርመኛል። ስለ ሜሎዲ ስራዎች እንዲ ባጭሩ ተወርቶ የሚያልቅ አይደለም። ባጭሩ ሜሎዲ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል ከምንል ኢትዮጵያውያን በላይ ስለኢትዮጵያውያን መበደል እና መጨቆን እያጋለጠች የምትገኝ፤ ምስጋና እና ክብር የሚገባት ድንቅ ሰው ናት ።
ውዷ ሜሎዲ እነሆ የከበረ ምስጋናዬ ይድረስሽ! ያሰብሽው ሁሉ ይሳካልሽ!

Kenya talks to Ethipoia over Oromo River dam

Nairobi (The Star) — Most scientists say the Ethiopia dams will starve Lake Turkana of water and eventually kill it. Negotiators to find lasting solution
Foreign Affairs CS Amina Mohamed during a media briefing at Harambee House, Nairobi, on October 14, 2013 / HEZRON NJOROGE
Foreign Affairs CS Amina Mohamed during a media briefing at Harambee House, Nairobi, on October 14, 2013 / HEZRON NJOROGE
Kenya has restarted negotiations with the Ethiopean government to find a long lasting solution over the Gibe III Dams, which threaten Lake Turkana’s existence.
Foreign Affairs Cabinet Secretary Amina Mohamed said the negotiators are discussing scientific findings and will soon reach a solution.
Most scientists have opposed the dams Ethiopia is building on River Omo, saying they will starve Lake Turkana of water and slowly kill it.
Lake Turkana is the world’s biggest desert lake and supports more than three million Kenyans.
Mohamed said the negotiations will strike a balance between Ethiopea continuing to explore ways of meeting their energy demands and the impacts of the project on the Turkana basin.
Ethiopia wants to make hydropower its major national export, but climate change and ecological degradation could have a serious problem to the Turkana lake basin.
Kenya a few years ago signed an agreement to buy electricity from Ethiopia after the Gibe Dams are complete.
The dams and expanded large irrigated plantations in the lower Omo basin have been a major issue that will threaten the food security and economy of millions of people, especially on the shores of Lake Turkana.
Mohamed said climate change is a serious matter and awareness must be raised if its effects are to be mitigated.
“We as a country have done a lot in as far as addressing climate change issues is concerned. The message will be clear, the journey as a country has been long, but we have participated through our mission in New York,” she said.
Mohamed spoke at the ongoing second UN Environment Assembly in Gigiri, where she launched prototype postal stamps depicting 17 Sustainable Development Goals.
The Postal Corporation of Kenya designed the stamps and the UN provided financial support.

በጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ላይ የቀረበው የሽብር ክስ ዝርዝር Ethiopia Human Rights Project

የፌደራል አቃቤ ህግ ግንቦት 10/2008 ዓ.ም በተጻፈ የክስ ማመልከቻ የሽብር ክስ የመሰረተበት የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ላይ የቀረበው ክስ የጸረ ሽብር አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 7(1) ላይ የተመለከተውን የወንጀል ድርጊት መተላለፍ የሚል ነው፡፡
Getachew Shiferaw
ተከሳሹ ከ24/05/2006 ዓ.ም እስከ 13/04/2008 ዓ.ም ድረስ ባሉት ጊዜያት ግንቦት ሰባት ከተባለ የሽብር ድርጅት አመራሮች ጋር በማህበራዊ ድረ ገጽ በተለይም ፌስቡክ እና ስልክ ግንኙነት በመፍጠር ለሽብር ቡድኑ ተልዕኮ የተለያዩ መረጃዎች በማስተላለፍና በሽብር ድርጅት ውስጥ መሳተፍ ወንጀል ፈጽሟል ሲል አቃቤ ህግ በክሱ ላይ ጠቅሷል፡፡
በአቃቤ ህግ ክስ ላይ እንደተመለከተው ተከሳሽ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው በህግ ተመዝግቦ በሀገር ውስጥ ህጋዊና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚያደርገው ሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ያደረገው የመልዕክት ልውውጥ ክስ ሆኖ ቀርቦበታል፡፡
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ከተለያዩ ውጭ ሀገር ከሚገኙ ሚዲያዎች ባለሙያዎች በተለይም ኢሳት ጋር ያደረጋቸው ቃለ-መጠይቆችና የመረጃ ልውውጦችም በሽብር ክስነት ቀርበውበታል፡፡ ተከሳሹ በሽብርተኝነት ክስ ተከሰው በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎች ቤተሰቦቻቸውን እንዴት ማገዝ ይቻላል በሚል ከዳያስፖራ አባላት ጋር በማህበራዊ ድረ ገጽ የተለዋወጣተቸው መልዕክቶችም በክሱ ላይ ተካተው ቀርበዋል፡፡
በአጠቃላይ ጌታቸው ‹‹…በተለያዩ አካባቢዎች ከሚገኙ የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር እየተገናኘ መረጃ በመሰብሰብ በውጭ ሀገር ለሚገኙ የሽብር ቡድኑ አመራሮች መረጃ በማስተላለፍ….›› በሽብር ድርጅት ውስጥ በማናቸውም መልኩ መሳተፍ ወንጀል ክስ ቀርቦበታል፡፡
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ለአምስት ወራት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቆይቶ ባለፈው ሳምንት ክስ ተመስርቶበት ቂሊንጦ በእስር ላይ ይገኛል፡፡ ግንቦት 26/2008 ዓ.ም የቀረበበት ክስ በፍርድ ቤት ሊነበብለት ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡

Monday, May 30, 2016

Proposed Ethiopia Law Worries Bloggers, Activists (VOA)

For years, the Ethiopian government has been accused of using its anti-terrorism law to crack down on internal political dissent. Now, bloggers and political activists worry freedom of expression could be limited even further by a proposed new law.

Bildergebnis für voa
Critics of the new legislation, called the Computer Crime Proclamation, say it would widen the door for the Ethiopian government to punish individuals voicing their opinions on the Internet.government to punish individuals voicing their opinions on the Internet.
Daniel Berhane, a prominent blogger who also runs his own website, believes the provisions against cybercrime in the bill could be used against anyone expressing an opinion online.
“This computer crime proclamation denies me the defenses, the safeguards already provided in the criminal code and the mass media law,” he said. “So it’s simply more prohibitive than the existing laws and it does that with just one sentence.”
The new bill mostly focuses on cybercrime and security; but, the proclamation also allows the imprisonment for those who distribute mass emails and it gives the national intelligence service the power to conduct virtual investigations without approval from a judge.
Belayhun Yirga of Ethiopia’s Ministry of Justice said nothing will change for those who are expressing their views on the Internet.
“If that person is just explaining his opinions or his view, he will not be liable for crime; but, the target of this law is just on the intention of the activity of the people concerning defamation,” he said. “If their purpose and general goal is for defaming, they will be liable because defamation, it is a crime.”
Ethiopia is often criticized for detaining, arresting and imprisoning individuals who voice their opinions online.
Journalist and blogger Eskinder Nega is currently serving an 18-year sentence. A group of young bloggers known as Zone 9 was detained for over a year.
And Yonathan Tesfaye, the spokesperson of an opposition group, has been in detention for nearly six months over comments he made on Facebook.
Haben Fecadu of human rights group Amnesty International says the Ethiopian government is currently using the 2009 Anti-Terrorism Proclamation to crack down on criticism.
“The precedent set by Yonathan’s charges are disturbing because it allows for the government to go after someone for expressing their views over social media,” he said. “Yonathan was also charged under the Anti-Terrorism Proclamation, and evidence against him was allowed to be presented and heard by the court without him knowing what that evidence was.”
The new Computer Crime Proclamation likely will be enacted in the next few weeks.

መንግስት ከ2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከአትላስ ኩባንያ ከተወሰደ በኋላ በኩባንያው ስር የነበሩ የባለሃብቶች ድርሻ ማሽቆልቆሉ ተገለጸ

መንግስት ከ2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከአትላስ ኩባንያ ከተወሰደ በኋላ በኩባንያው ስር የነበሩ የባለሃብቶች ድርሻ ማሽቆልቆሉ ተገለጸ

ኢሳት (ግንቦት 18 ፥ 2008)
በቅርቡ በኢትዮጵያ መንግስት ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ከሁለት ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ከቁጠባ ሂሳቡ እንደተወሰደበት ያስታወቀው የብሪታኒያው ኩባንያ ድርጊቱን ተከትሎ በኩባንያው ስር ለኢንቨስትመንት ፍላጎት የነበራቸው ባለሃብቶች ድርሻ ማሽቆልቆሉ ገለጸ።
ይኸው በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት በሽርክና በብርጭቆ ማምረት ላይ ተሰማርቶ የነበረው ኩባንያ በስሩ ኢንቨስት በማድረግ ፍላጎት የነበራቸው አካላት ድርሻ ከ30 በመቶ መቀነሱን ይፋ አድርጓል።
አትላስ አፍሪካ የተሰኘው ኩባንያ በሽርክና አብሮት የሚሰራው ድርጅት ከዚህ ቀደም ከታክስ ክፍያ ጋር በተያያዘ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ውዝግብ ውስጥ መቆየቱን አውስቷል።
ይሁንና፣ ኩባንያው ሽርክናውን ከጀመረ በኋላ የታክስ ክፍያው እሱን እንደማይመለከተው መግባባት ቢኖርም፣ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በህገወጥ መንገድ 2.4 ሚሊዮን ዶላርን ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሂሳቡ ውስጥ መውሰዱን አመልክቷል።
በኩባንያውና በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎም በኩባንያው ስር በሃገሪቱ ኢንቨስት ለማድረግ የነበራቸው አካላት እምነት ማጣታቸውንና ድርሻውም 30 በመቶ እንደቀነሱ ድርጅቱ በድረገጹ ላይ አስፍሯል።
በህገወጥ መንገድ ተወስዶብኛል ያለውን ገንዘብ ለማስመለስም፣ ኩባንያው ፖለቲካዊና ዲፕሎማቲክ አማራጮችን እየወሰደ መሆኑንም በቅርቡ መግለጹ ይታወሳል።
አትላስ አፍሪካን ኢንተርፕራይዝ ሃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ቲፕ [TEAP] ከተሰኘ ሃገር በቀል ኩባንያ ጋር ሽርክና በመግባት ለዳሽን ቢራ ብርጭቆዎችን እያመረተ እንደሚገኝ ታውቋል።
በሌሎች ተመሳሳይ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንደነበረው የገለጸው ኩባንያው 2.4 ሚሊዮን ዶላሩ ከመንግስት ጋር ተደርጎ የነበረን ስምምነት የሚሰጥ ተግባር እንደሆነም አክሎ አመልክቷል።
የኩባንያውን ቅሬታ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል እስካሁን ድረስ የተሰጠ ምላሽ የሌለ ሲሆን፣ ኩባንያው የተለያዩ አማራጮችን እየተከተለ እንደሆነም አመልክቷል።

ጁን 4፥ 2016 የሚያካሂደዉን የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሰሜን አዉሮፓ አቀፍ ህዝባዊ ውይይትና የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በተመለከተ የተሰጠ አጭር ጋዜጣዊ መግለጫ

ጁን 4፥ 2016 የሚያካሂደዉን  የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሰሜን አዉሮፓ አቀፍ ህዝባዊ ውይይትና የገቢ ማሰባሰቢያ  ዝግጅት በተመለከተ የተሰጠ አጭር ጋዜጣዊ መግለጫ

Patriotic Ginbot 7, Norway, Oslo
ሃገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ካለችበት ውስብስብ ችግር ለመታደግ ለሃገሪቱና ህዝቧ ቅን የሚመኝ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁሉ ህወሓትን ለማስወገድ በሚደረገዉ ተግባራዊ ትግል ውስጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መሳተፍ የሚኖርበት ወቅት ላይ እንገኛለን።
ኢትዮጵያ በአጣብቂኝና በመንታ መንገድ ላይ በምትገኝበት በዚህ ወሳኝ ወቅት ከዳር ሆኖ መታዘብ ዘረኛውን፣ አምባገነኑንና፣ ፋሽስቱን የህወሓት አገዛዝ ከመደገፍ ተለይቶ እንደማይታይ ብዙዎቻችን እንስማማበታለን።
አርበኞች ግንቦት ሰባት  እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ህሊናውና አቅሙ በሚፈቅድለት የትግል ዘርፍ መሰማራት ይችል ዘንድ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ጥሪዉን ካስተላለፈ ሰንበት ብሏል። በዚህም መሠረት የህወሓትን አፈና በጠነከረ ክንድ ለመመከት የቆረጡ አርበኛ ታጋዮችና ከፍተኛ የአመራር ብቃት ያላቸዉን ምሁራን ጨምሮ በረሃ ወርደው የወያኔን አገዛዝ መፋለም ጀምረዋል። በግምባር መሰለፍ ያልቻሉት ደግሞ በገንዘባቸዉና በእዉቀታቸዉ የሚፈለግባቸዉን በማበርከት ላይ ይገኛሉ፣
ትግሉ የሚካሄደዉ ሃገሪቱን ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠረ፣ ብሎም የሃገሪቱን አንጡራ ሃብት፣እንዲሁም በልመናና በብድር የሚገኘዉን መዋእለ ንዋይ በማሟጠጥ ተቃዋሚዎቹን ለማጥፋት በሚንቀሳቀስ የወንበዴ ቡድንና ከሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ዉጭ ሌላ ምንም አጋር በሌለዉ የነጻነት ታጋይ መካከል ነዉ፣፣
ለነጻነት የሚደረግ ትግል እልህ አስጨራሽና አድካሚ ነዉ፣ ዉድ ዋጋና በገንዘብ የማይተመነዉን ህይወትም ያስከፍላል፣ዉጤቱ ግን ከሁሉም ነገር የበለጠና ዉድ ነዉ፣፣ በመሆኑም ይህ ወሳኝ ሐገርን የማዳን ጥረት ዉጤታማ እስኪሆን ድረስ ነጻነት ናፋቂ የሆን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ያላሳለሰና ሁለገብ ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅብናል፣፣
ይህንን መሰረት በማድረግ June 4, 2016 የሰሜን አዉሮፓ ሃገራትን ያማከለ  ታላቅ ህዝባዊ ዉይይትና የገቢ ማሰባሰብያ ፕሮግራም በኖርዌ ሃገር ኦስሎ ከተማ ተዘጋጅቷል፣፣
በዚህ ፕሮግራም ላይ የአርበኞች ግንቦት ሰባት የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ መሪ ታጋይ አርበኛ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከበረሃ በመንቀሳቀስ በመካከላችን በአካል በመገኘት ስለትግሉ ማብራሪያ ይሰጣሉ።
ፕሮግራሙ የተዘጋጀዉ ከተለያዩ የሰሜን አዉሮፓ ሃገሮች ተዉጣጥቶ በተቋቋመ ግብረ ሃይል ሲሆን በኖርዌ ሃገር በሚገኘዉ የዲሞክራሲያዊ ለዉጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት የበላይ አሰተባባሪነት ነዉ፣፣ በዚህ ታላቅ አህጉራዊ ስብሰባ ላይ በኖርዌይና በተለያዩ የሰሜን አዉሮፓ ሃገራት የሚኖሩ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በብዛት ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፣
ፕሮግራሙ ከየትኛዉም የአለማችን ክፍል ለሚመጣ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ወዳጅ ክፍት ነዉ፣፣ በተለይም በስካንዲኒቪያንና፣ በአጎራባች የአውሮፓ ሃገራት  የምንኖር ነጻነት ናፋቂ ዜጎች የፕሮግራሙ ታዳሚዎች በመሆን የበኩላችንን እንድንወጣ ግብረሃይሉ በትህትና ያሳስባል፣፣
በተለያዩ አህጉራት ያላችሁና በአካል መገኘት የማትችሉ ኢትዮጵያዊያን  ለዚህ ሃገር የማዳን ጥሪ የትግል አጋርነታችሁን በሚያመቻችሁ መንገድ ታሳዩ  ዘንድ አስተባባሪ ግብረ ሃይሉ በአክብሮት ይጋብዛል።
የፕሮጋራሙ ቀን፣ June 4, 2016 
ሰአት፣ ከ14፣00 ሰአት ጀምሮ
የፕሮግራሙ ቦታ፣ በቀጣይ የሚገለጽ ይሆናል
ተጋባዥ እንግዳ፣ የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከፍተኛ መሪ  ከኤርትራ
 ኢትዮጵያችን በክብር ለዘላለም  ትኖራለች!!
የዲሞራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
ሜይ 13፣ 2016 ኖርዌይ፣ ኦስሎ

ባለፈው 15 ቀናት ብቻ 2 ሴቶችና 5 ወንዶች የግንቦት 7 እና ኦነግ አባል ናችሁ ተብለው በአ.አ ኤርፖርት ታስረዋል

የጆሐንስበርግ ዲያስፖራ በሽብርተኛነት ተወንጅሎ ተያዘ
 ከልዑል ዓለሜ
ዛሬ ኮሽታዎች ሁሉ ያስበረግጡታል! ከምንም በላይ በሰፊዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያደረሰዉ ወንጀል ነግ በምን አይነት መልኩ እንደሚከፈለዉ ሲገምት ሰላም ይነሳዋል፤ ከንፈር ያልነከሰበት ልቡ ያላቄመበት በእርሱ በግፍ ያልተነካካ ባለመኖሩ ሁሉንም እየነከሰ በማቁሰል ዉድቀቱን እያፋጠነ ይገኛል::
አዎ እራሱን ህወሃት እያለ የሚጠራዉ የክፉዎች ስብስብ የሆነዉ የህዝብ ጠላት ወያኔ የሚመራዉ የብሔራዊ መረጃ ከኢትዮጵያ ዉጭ ወደ ሐገር ቤት የሚገቡ ኢትዮጵያዊያንን በማንገላታት በማሰርና በማፈን በእጅጉ ተጠምዷል፡ በመሆኑም ከአሜሪካ፣ ከኖርዌይና፣ ከሲዉዲን እንዲሁም ከደቡብ አፍሪካ የሚገቡ ወገኖቻችን የአዲስ አበባ ኤርፖርት ላይ በተቀመጠዉ የዚሁ የብሔራዊ መረጃ ቀኝ እጅ የሆነዉ እና በአንድ ብሔር ብቻ በተመሰረተዉ ኢሚግሬሽን ፖሊስ ቡድን ያለአግባብ እየተንገላቱ ይገኛሉ።

በዚህም የተነሳ በዚህ ባሳለፍነዉ 15 ቀናት ብቻ 2 ሴቶችና 5 ወንዶች የአርበኞች ግንቦት 7 እና የኦነግ አባል ናችሁ ተብለዉ ከአዲስ አበባ ኤርፖርት ተጠልፈዉ በሽብር ወንጀል ተከሰዋል:: ከነዚህም መካከል ሙሉጌታ የተባለ ከየትኛዉም የፖለቲካ ድርጅት ጋር ግንኙነት የሌለዉ ነዋሪነቱ በደቡብ አፍሪካ የሆነና ጆሐንስበርግ ሞል በተባለ የንግድ መአከል ዉስጥ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ስራ ላይ የተሰማራ ግለሰብ በነዚሁ ወንጀለኛና የወያኔ ቡድኖች እጅ መዉደቁን ምንጮች ጠቁመዋል። 

ሙሌጌታ ከጆሓንስበርግ ኦሊቨር ታምቦ ኢንተርናሽናል ወደ አዲስ አበባ ከገባበት ወቅት አንስቶ የብሔራዊ መረጃ ቡድን አባላቶች ግለሰቡን ሲከታተሉት እንደነበረ ምንጮች የጠቆሙ ሲሆን በተለይም በወያኔ ቀንደኛ ደጋፊዎች እና በትግራዩ ቡድን ኢንባሲ ደቡብ አፍሪካ አዲስ የተቋቋመዉ የዲያስፖራ ኢንጌጅመንት አሶሴሽን ደቡብ አፍሪካ ( Diaspora engagement association in south Africa ) የተባለ መሐበር ስለ ግለሰቡ ለወያኔ የብሔራዊ መረጃ የሰጠዉ የተሳሳተ ማንነት ምክንያት ግለሰቡ እንዲታፈንና በትናንትናዉ እለት የአርበኞች ግንቦት 7 አባል እንዲሁም ለደቡብ አፍሪካ አርበኞች የግንቦት 7 አባላቶች መልእክት ይዞ ሲሄድ ተያዘ በሚል የሐሰት ክስ በሽብር ወንጀል ተከሶ ዘብጥያ ተወርዉሯል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

የወልቃይት ጠገዴ፣ ቃፍቲያ፣ ሁመራና ጠለምት ህዝብ ፈጥኖ ደራሽ አጋር ይሻል! (አስቸኳይ መግለጫ)

ጎንደር ህብረት – አስቸኳይ መግለጫ
ወያኔ ገና ካፈጣጠሩ ጀምሮ፤ አገር ሸንሽኖ፤ ህዝብን ከፋፍሎ፤ ለዘለዓለም የሥልጣን ዘመኑን ለማራዘም አለሞ እና ሸርቦ የተነሳውን ህልሙን ለማሳካት፤ የመጀመርያ የጥቃት ኢላማው ያደረጋት የጎንደር ክ/ሀገርን ነው። የዚም የመጀመርያው የግፍ ሰቆቃን እየተጋቱ ያሉት፤ ደግሞ ሰሜን ምዕራብ ክ/ሀገራችን ኗሪ የሆኑት የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ፀለምት ወገኖቻችን ናቸው።ye gondar hibret
ይሁን እንጂ፤ ከሰላሳ ዓመት በላይ የአካባቢዋን እና የዘር መሰረታቸውን ታሪክ ነጋሪ እንኳ እንዳይኖር፤ አንድ በዓንድ ለቅሜ አጥፍቻለሁ፤ ብሎ ያስብ የነበረውን ከንቱ የወያኔ ቅዠት አዲሱ ትውልድ፤ ለማንነቱ፤ ፍርሃትን ሰብሮ ወደ ትግል ከወጣ ውሎ ቢያድርም፤ አሁን ግን የነዚህ ወገኖቻችን የትግል ምዕራፍ የመጨረሻው የሞት ሽረት ደረጃ ላይ ደርሷል።
የዚህም አንዱ እና ዋንው ሀቅ፤ ወያኔ በጎንደር ህዝብ ላይ በጉልበት የጫነዉ የመስፋፋት እና የመሬት ቅርምት አባዜን ለመገደብ፤ በሁሉም የጎንደር ሕዝብ ቆራጥነት ድጋፍ ማግኘቱ ነው። ከእንግዲህ በኋላ፤ የቃፍቲያ ሁመራ፤ ወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት ህዝብ የወያኔን የዘር አጥፊ በደል መሸከም ከሚችለዉ በላይ በመሆኑ፤ ትግስቱን ጨርሶ በአንድ ድምጽ ተማምሎ “የትግራይ ነፃ አዉጭ ግንባር ተከዜን ተሻግሮ አያስተዳድረንም” ከሚል ዉሳኔ ላይ ደርሶ፤ የራሱን መሪና የጎበዝ አለቃ መርጧል። በጎንደሬነቱ፤ በአማራነቱ፤ በባህሉ፤ ለዘመናት በኖረበት መሬቱና በጠቅላላ ማንነቱ ላይ ግፍና መከራ ስለተፈጸመበት፤ በአንድ ድምጽ በቃለ መሃላ ነጻነቱን አዉጇል። ተወደደም፤ ተጠላም፤ ይህ የቃፍቲያ ሁመራ ወልቃይት፤ ጠገዴ፤ እና የጠለምት ህዝብ “ጎንደሬም አማራም ነን” በሚል መፈክር ለነፃነቱ ያቀጣጠለውን ትግል፤ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በቅንነት መቀበል ሰባአዊነት ነው። በተለይ ደግሞ፤ ለዘመናት የጎንደር እና የትግራይ ሕዝብ፤ በጉርብትና ሲኖሩ፤ ተዋደው እና ተፈቃቅረው ያጋኙትን ተካፍለው ከመኖር ባሻገር፤ አንድም ቀን እንኳ፤ የመሬት ይገባኛል ግጭት አድርገው እንደማያውቁ እየታወቀ፤ በአሁኑ ሰዓት፤ የትግራይ ወገኖቻችን፤ ዘመን ካሳበጣቸው፤ ጥቂት ከውሥጣቸው በወጡ ቡድኖች ምክንያት፤ የተጠነሰሰውን፤ ታሪክን መሰረት ያላደረገ፤ የመሬት ሥግብግብነት፤ ተንኮል፤ በዝምታ፤ መመልከት፤ እጅግ አሳዛኝ የሆነ፤ የታሪክ ስህተት መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን።
ስለሆነም፤ የትግራን እና የጎንደርን ሕዝብ የወደፊት አብሮነት ታሪክ ለማስቀጠል ሲባል፤ ማንኛውም የትግራይ ተወላጅ፤ ወገኖቻችን ይዘው የተነሱበትን የማንነት ጥያቄ፤ የታሪክ እውነት መሆኑን፤ ማክበር እና መቀበል እንዳለበት ከወዲሁ ልናሳስብ እንወዳለን። አፈጣጠሩ እና ባህሪው አይፈቅድለትም እንጂ፤ ልብ ሰጥቶት የገዥዉ መደብም ቢሆን፤ ይህን የሕዝብ ውሳኔ ማከበር የጎንደርን ህዝብ ማክበር ነዉ የሚል እምነት አለን። ለዓመታት የጠዬቀዉ የጎንደሬነት ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ ጭቆናዉ በዝቶበት እራሱ በመረጣቸዉ መሪወች ለመተዳደር መወሰኑ ፍህታዊ እና ህዝባዊ እርምጃ ነዉ። መከበር ይገባዋል!!
ከእንግዲህ ይህንን ህሊናዉ የቆሰለ እንግዳ ተቀባይ ደግ ህዝባቸን ላይ፤ ተከዜን ተሻግሮ ከአድዋ በመጣ ፀረ ሽምቅ ሰራዊት ተኩሶ በመግደል፤ የበለጠ ሕዝባችንን ወደከፋ መተላለቅ የሚገፋ መሆኑን ተገንዝቦ፤ ጣቱን ከመሳሪያ ምላጭ አንስቶ፤ የወገኖቻችን ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲሰጥ እናሳስባለን።
ይህ ግፍ እና በደል የወለደውን፤ የጎንደሬ/የአማራ ማንነት ጥያቄ፤ ቆመንለታል ብላችሁ፤ ለ25 ዓመት በወያኔ፤ እየተሽከረከራችሁ ያላችሁ፤ የብ.አ.ዴን አባላት እና ካድሬዎች፤ የማንነታችሁ መፈተኛ ወቅት ላይ በመሆናችሁ እና፤ የመጨረሻ እጣ ፈንታችሁ ወቅት ላይ በመድረሳችሁ፤ ከእንቅልፋችሁ የምትነቁበት ደወል፤ እየተደወለ ነው። በዚያው እንዳታሸልቡ፤ ከወገኖቻችሁ ጋር ለማንነታችሁ አብራችሁ በመቆም እስካሁን የበደላችሁትን ወገናችሁን ልትክሱ የግድ ነው። እንዲሁም፤ የሰባቱ አዉራጃ የጎንደር ህዝብ፤ ጥያቄው፤ የራሱ ማንነት ጭምር መሆኑን በማመን፤ በአስቸኳይ፤ በሚፈለገው ሁሉ ትብብሩን ማሳየት፤ የግድ እሚልበት ደረጃ ላይ በመሆኑ፤ እስቸኳይ ታሪካዊ ምላሽ፤ ለወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት ወገኖቻችን እንዲያሳይ የጎንደር ሕብረት ታሪካዊ እና ወቅታዊ ጥሪያችንን ለማስተላለፍ እንወዳልንለን። የጎንደር ሕብረት የተመሰረተበት ቋሚ ዓላማም፤ ሁላችንም በሰላም እና በፍቅር ታሪካዊ፤ መልካዓ ምድራችንን ጠብቀን በጋራ እንድንኖር የሚያስችለንን ታሪክ ለማስጠበቅ ነው። በመሆኑም፤ ስማችን ጎንደር ነክ ይሁን እንጅ፤ ለትግራይም ሆነ፤ ለመላ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን እኩል ፍቅር፤ እኩል፤ ተቆርቋሪነት እና ኃላፊነት ይሰማናል።
ሌላዉ ሳንጠቅስ የማናልፈዉ እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ ደግሞ ባለፈው ወር የጋምቤላ ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመዉ የጀምላ ጭፍጨፋ ነዉ። የኢትዮጵያን መሬት አሳልፎ ለመስጠት በተሸረበ ሴራ ምክንያት ወያኔ፤ ጠረፍ ጠባቂ፤ ፀጥታ አስከባሪ፤ የነበሩትን የታጠቁትን የአካባቢ ሚሊሻዎች፤ ትጥቃቸውን አስፈትቶ፤ ካምፕ ውስጥ እንደከብት በመዝጋቱ ምክንያት፤ አካባቢዉን ክፍት መሆኑን የተረዱ፤ ከ እንሰሳት ዝርፊያ አልፈው የሰው ህይወት ለማጥፋት ተዳፍረው የማያውቁ የደቡብ ሱዳን ኗሪ የሙርሊ ብሔረሰቦች በወሰዱት አሰቃቂ ርምጃ ከ200 በላይ ኢትዮጵያዊያን ተጨፍጭፈዉ፤ 150 ታፍነዉ ሲወሰዱ፤ እጅግ ብዛት ያላቸውን ቤት እና ንብረት አቃጥለው፤ በሺ የሚቆጠሩ የቀንድ እና የጋማ ከብቶችም ተዘርፈው ተወሥደዋል።
እንዲሁም በተመሳሳይ መልኩ በመተከል ቁጥራቸዉ ወደ 70 የሚደርሱ አርሶ አደሮች በሱዳን መንግስት ተጠልፈዉ መዳረሻቸዉ ጠፍቶ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ የቀንድ ከብቶችም ተዘርፈው ሲወሰዱ፤ እርምጃ የሚወስድ ቀርቶ፤ የሚጠይቅ መንግስት እንኳ አልተገኘም።
ይህ የሚያሳየው፤ አገራችንም ሆነ ሕዝባችን፤ መንግሥት ተብዬ አገር በቀል ጠላት ቅንብር፤ በውጭ ታሪካዊ ጠላቶቻችን የጥቃት አደጋ እንደተደቅነብን ነው። በመሆኑም፤ ኢትዮጵያ አገራችንም ሆነ የህዝባችን ደህንነት የሚጠብቅ መንግስት እንደሌለ አዉቀን በሞቱት ወገኖቻችን መሪሪ የሆነ ሃዘናችንን በሃገራዊ ቁጭት እየገለጽን፤ ለዘመድ አዝማድ ሁሉ መጽናናትን ይስጥልን እንላለን። የደቡብ ሱዳንም ሆነ የሰሜን ሱዳን መንግስት በወያኔ ቅጥረኞች ታፍነዉ የተወሰዱ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ከነንብረታቸዉ ወዳገራቸዉ በአስቸኳይ እንዲመለሱ፤ ወንጀለኞችም ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን። የመላዉ ኢትዮጵያ ህዝብም፤ በዬአካባቢው የራሱን መሪ መርጦ፤ ደህንነቱን ጠብቆ፤ ዳር ደንበሩን እንዲያስከብር ጥብቅ መልክታችን እናስተላልፋለን። ከዉጭ አገር ጋር ተባባሪ የሆነዉ የወያኔን መንግስት እንደ አገር መሪ ቆጥሮ ህዝባችን እንዳይዘናጋ አደራ እንላለን።
በመጨረሻም በጎንደር ክፍለ ሀገር በቋራ ወረዳ የጓንግን ወንዝን ተሻግሮ ከኢትዮጵያ መሬት የሰፈረዉ የሱዳን ወታደር በአስቸኳይ እንዲለቅ እንጠይቃልን።
ጀግናዉ የጎንደር ህዝብ ዳር ድንበሩን ያስከብራል!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!
ጎንደር ህብረት

የትምባሆ ሞኖፖል ለጃፓን ኩባንያ ተሸጠ

የትምባሆ ሞኖፖል ለጃፓን ኩባንያ ተሸጠ

tobaco

የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብትና ንብረት የሆኑትን መሸጥና መዝረፍ መለያ የሆነው የወያኔ አገዛዝ ከአጼ ኃይለስላሴ ዘመን ጀምሮ በሕዝብ ሀብትነት የተመዘገበውን የትንባሆ ሞኖፖል ለጃፓኑ ኩባንያ መሸጡ ታውቋል። ወያኔ የሽያጩን ውል በሚመልከት ከኩባንያው ጋር በቅርቡ አንድ ውል ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ትምባሆ ሞኖፖልን ለመግዛት አንድ የእንግሊዝና የአሜሪካ ኩባንያ 230 ሚሊዮን ዶላር አቅርበው እንደበርም ታውቋል። ጄቲ የተባለው የጃፓን የትንባሆ ኩባንያ ግዥውን መፈጸሙን ሲገልጽ በአፍሪካና በመካከለኛ ሰፊ ገበያ እንዳለውም ተገልጿል። የወያኔ አገዛዝ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ ጀመሮ በሕዝብና በአገር ስር የነበሩ ንብረቶችን በመሸጥ የወያኔ መሪዎችን ያከበረ መሆኑ ይታወቃል።

የፓርቲ ፖለቲካ የትግል እርሻ – (ከዘላለም ክብረት እና በፍቃዱ ኃይሉ)

weyeyet
ከጠዋቱ ጤዛ እስከ ምሽቱ ቁር
አንጋው ተገኝ በሠላሳዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለ ወጣት ነው። ፀጉሩን ያጎፍራል። ሲናገር በብዙ ነገሮች እየተደነቀ ነው። አንጋው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የሰሜን ጎንደር አብረሃ ጅራ ወረዳ ኃላፊ በመሆን እጅግ ፈታኝ ጊዜያትን አሳልፏል። የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ የሀገሪቱ ክፍሎች መንቀሳቀስ የሚያስከፍለው ዋጋ ከባድ መሆኑን ደጋግሞ ይናገራል። የፓርቲው አመራር ሁኖ በሠራበት ወቅት ፓርቲ ስብሰባ እንኳን ማድረግ እጅግ ከባድ መሆኑን ያስታውሳል። ፖሊስና የደኅንነት ኃይሎች አመራሮቹን እየተከታተሉ ሲያስጨንቋቸው ‹የፓርቲው ሥራ ከሚቆም በሚል አንገረብ ወንዝ ወርደን እየዋኘን እንሰበሰብ ነበር› ይላል። እየዋኘን ሰው ወደኛ በመጣ ቁጥር እየተበታተንን፤ ሰው ራቅ ሲልልን ደግሞ እዛው ውኃው ውስጥ ሰብሰብ ብለን እየተንሳፈፍን ነበር ስብሰባ የምናደርገው የሚለው አንጋው በፓርቲ እንቅስቃሴ ምክንያት ስድስት ጊዜ ከሥራ ተባሮ ስድስት ጊዜ መመለሱን ሲገልጽ አንዳንዴ በሕይወት መቆየቴም ለኔ ግርም ይለኛል እያለ ነው። ይባስ ብሎ በሠላማዊ ትግል ቆርቦ በዚህ ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ የነበረው አንጋው ተገኝ የሰውም ሆነ የሰነድ ማስረጃ ሳይቀርብበት አሁን ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር ግንኙነት አለህ በሚል ምክንያት በመጨረሻ ለእስር የተዳረገ ሲሆን፤ እስር ቤት ሁኖም የታገለለትና የደከመለት አንድነት ፓርቲ ሲፈርስና በእሱ አባባል ‹መፈንቅለ አመራር› ሲካሄድበት ተመልክቶ ያዝናል። ለዚህ ሁሉ መሆን አንጋው ተጠያቂ የሚያደርገው ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን ነው። ‹ሕግ የማይገዛው መንግሥት› እያለ ሁሌም ይገረማል። ይህ የኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ ችግር የገዥው ፓርቲ ቅጥ ማጣት ነው ከሚሉት ወገን የሚቀርበው ሐሳብ ትክክለኛ ተምሳሌት ነው።
ከዚህ አሳዛኝ ኹነት መለስ ብለን አርብ ሚያዚያ 28፣ 2008 ከጠዋቱ 4፡30 እስከ 5፡30 ድረስ በአንድ ሰዓት ውስጥ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጆች ለጽሑፉ ግብዓት የሚሆን መረጃ ለማግኘት በማሰብ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ መሠረት እንዲሁ አለፍ አለፍ እያልን በአሁኑ ወቅት በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው ከሚገኙ ሰባ አምስት ፓርቲዎች መካከል የሃያ አምስት የተቃዋሚ ፓርቲዎች የስልክ አድራሻ ላይ ስልክ የደወልን ሲሆን፤ ከሃያ አምስቱ ሙከራዎች መካከል ሁለቱን ስልኮች ያነሱልን ሕፃናት ሲሆኑ፣ የሰባቱ ስልክ ቢጠራም አይነሳም፤ የዐሥራ አምስቱ ስልክ ደግሞ ከነአካቴው የማይሠራ ሲሆን፤ የአንዱ ብቻ ማለትም ‘የኦሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ሕብረት’ ስልክ ላይ የፓርቲውን አመራር ልናገኝ ችለናል። በተመሳሳይ ጊዜ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ያደረግነው ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪም ስልኩ ሊነሳ ባለመቻሉ ማብራሪያ ማግኝት አልቻልንም። እንግዲህ ‹የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ ሰሞን ግርግር ከመፍጠር ያለፈ ምንም አይፈይዱም የሚለው ሐሳብ እንዲሁ ያለውን ሁኔታ ቀረብ ብሎ ካለማየት የሚመጣ ነው› የሚሉ ተችዎችም ሁሌም የሚፈተኑበት ጉዳይም ይሄው ተቃዋሚ ፓርቲ ተብለው የተመዘገቡት ፓርቲዎች በሚገባቸው ቦታ አለመዋላቸው ነው። ፓርቲዎቹ የስልክ እንኳን አድራሻ የሌላቸው/ቢኖራቸው እንኳን የማይሠሩ ስልኮችን ይዘው ለኢትዮጵያ ሕዝብ የለውጥ መሠረት ይሆናሉ ብሎ ማሰቡንም ያከብደዋል። ይህ ደግሞ ተቃዋሚዎች የራሳቸው ሥራ ሳይሠሩ ገዥውን ፓርቲ ማውገዛቸው ተገቢ አይደለም የሚለው ሐሳብ ተምሳሌት ነው።

የጠዋቱ ጤዛ
‹የፓርቲ ፖለቲካ ማለት በሕግ የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ራሳቸውን አደራጅተው ለምርጫ የሚያደርጉት ትግል ነው› የሚለው ጠቅለል ያለ ትርጉም በኢትዮጵያ ፖለቲካ አኳያ ይሠራል ማለት ከባድ ነው። ከተመዘገቡት የፖለቲካ ፓርቲዎች በማይተናነስ መልኩ የራሳቸው ፍላጎት እና ዓላማ ያላቸው ብዙ ቡድኖች ራሳቸውን የፖለቲካ ፓርቲ ብለው ሰይመው የሚንቀሳቀሱ ከመሆናቸው አንፃር የፓርቲ ፖለቲካ ከኢትዮጵያ ዐውድ አንፃር ለምርጫ የሚደረግ ሠላማዊ ትግል ነው ከሚለው ትርጉም ፈቅ ያለ መሆኑንም ነው እነዚህ ፓርቲዎች የሚያስረዱን።

በቡድን ተደራጅቶ የፖለቲካ ፓርቲ የሚባል ድርጅት ፈጥሮ መንቀሳቀስ የተጀመረው ኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲ ሞዴል (Party Political Model) የፖለቲካ ሒደት ከመጀመሯ ብዙ ቀደም ብሎ እንደሆነ የተለያዩ ጸሐፊዎች ያመላክታሉ። ከጣሊያን የአምስት ዓመታት ቆይታ በኋላ በተለይም ውጭ አገር ቆይተው የተመለሱ ኢትዮጵያዊያን በአውሮፓና በአሜሪካ ካዩት አሠራር በመነሳት የፓርቲ አደረጃጀት ኑሮ ፖለቲካው በዛው መሥመር እንዲቃኝ መፈለጋቸው አልቀረም። ዘውዴ ረታ ‹የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት› ባሉት መጽሐፋቸው በመጋቢት 1939 ንጉሠ ነገሥቱ ራሳቸው ስለ አገራችን ጠቅላላ ሁኔታና ስለ እኛ አመራር ሐሳባችሁን አቅርቡልኝ ባሉት መሠረት በወቅቱ የጽሕፈትና የሀገር ግዛት ሚኒስትርነትን ደርበው ይዘው የነበሩት ጸሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ ከሦስቱ የማሻሻያ ሐሳብ አቅራቢዎች መካከል አንዱ ነበሩ። በወቅቱ ወልደጊዮርጊስ የፖለቲካ ፓርቲ ለመመሥረት እየተንቀሳቀሱ ነው የሚል ሐሜት ይሰማባቸው ስለነበር ይሄን ሐሜት “እኔና አቶ መኰንን [ሀብተወልድ] እየተግባባንና እየተረዳዳን በመሥራታችን የፖለቲካ ፓርቲዎች በመሆናቸው ነው እየተባለ የሚነገርብን ደህና አድርገን እናውቀዋለን። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚያውቁት፤ የፖለቲካ ፓርቲ በአገራችን የለም።” በማለት ካስተባበሉ በኋላ ስለፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት ሲያስረዱ “እኔ በዚያ በመከራው የስደት ዘመን እንዳየሁት፤ ዛሬ በአለንበት ሰዓት ለኢትዮጵያ አስተዳደር እንደ እንግሊዝ አገር፤ ንጉሥ የታሪክና የባሕል የበላይ ጠበቂ ሆኖ ይነግሳል፤ መንግሥት ደግሞ በፓርላማ ሕዝብ ቀጥታ ከመረጠባቸው እንደራሴዎች መካከል በፖለቲካ ፓርቲ አሸናፊ የሆነው ይመረጣል፤ የሚለውን ሐሳብ ወስዶ መጠቀም ይቻላል ብዬ አላምንም። እንደ እንግሊዝ አገር መሆን እንችላለን ብሎ ማሰብ፤ አቅምን ካለማወቅ የተነሳ በሸንበቆ ላይ እንደሚገነባ ምኞት የሚቆጠር ይሆናል” በማለት ነበር። ይህ ሐሳብ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ለቀጣዮቹ ሃያ ሰባት ዓመታት ንጉሠ ነገሥቱ የፖለቲካ ፓርቲ የሚባለውን አደረጃጀት በጥርጣሬ እንደተመለከቱት ከመንበራቸው ሳይወዱ በግድ ተወገዱ። በንጉሠ ነገሥቱ ዘመን የፖለቲካ ፓርቲ የማቋቋምም ሆነ የፓርቲ ፖለቲካን ለማካሄድ የሚያስችል ምንም ዓይነት የሕግ ማዕቀፍም ሆነ ቀናነት ያልነበረ ቢሆንም የፓርቲ ቅርፅ ያላቸው አደረጃጀቶች በተለይም በመጨረሻዎቹ የንጉሡ አምስት የሥልጣን ዘመናት አቆጥቆጠዋል። አንትሮፖሎጅስቱ ዶ/ር ወንድወሰን ተሸመ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የፖለቲካ ፓርቲ የዛሬ ሃምሳ ዓመት በ1958 የተመሰረተው ‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ካውንስል› ነው የሚሉ ሲሆን፤ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ እዚህም እዚያም ማቆጥቆጥ የጀመሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች ላለፉት ሃምሳ ዓመታት ሲወጡና ሲወርዱ ቆይተዋል።

ከንጉሠ ነገሥቱ ስርዓት ማብቃት ጋር ተያይዘው ብቅ ብቅ ያሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች በግራ የፖለቲካ አስተሳሰብ የተቃኙና በፍጥነት ወደመጠፋፋት በመዝለቃቸው ተስፋ የተደረገበትን የፓርቲ ፖለቲካ አካሔድ እዛው ካለበት ላይንቀሳቀስ ተተክሎ ቆይቶ ከኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ወደ ሥልጣን መምጣት ጋር ተያይዞ አዲስ ተስፋ በብዙዎች ዘንድ ማደሩ አልቀረም። ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ከሚወደስባቸው ጉዳዮች አንዱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን (multi-party system) በሕግ ተቀብሎ በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ሕጋዊ ዕውቅና የሚሰጥ ስርዓት መዘርጋቱ ነው።
የሃምሳ ዓመታት የሙከራ ታሪክ፤ የሃያ አምስት ዓመታት ሕጋዊ ዕውቅና ያለው የፓርቲ ፖለቲካ ከዕድሜው አንጻር ምን ትርፍ አመጣ? ለምንስ ፈተናና እክል በየቀኑ እያጋጠመው ይወድቃል የሚሉት ጥያቄዎች መሠረታዊና የወደፊቱን ለመረዳት የሚረዱ ናቸው። በኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ እንዳያብብ እና እንዲቀጭጭ ምን እክል አጋጠመው? ለሚለው ጥያቄ አንድ ዓይነት ምላሽ መስጠት አስቸጋሪ ነው። ምክንያቱም እንደ መላሾቹ የተለያ መልሶችን እናገኛለን።

ዴሞክራሲ የማያበቅል መሬት?
የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሒደት በቅርበት የሚከታተሉ ምሁራን ለፓርቲ ፖለቲካ ስኬት ማጣትና ብሎም ዴሞክራሲ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይደረጅ መሠረታዊውን አስተዋፅኦ ያደረገው የመጠላለፍና አምባገነኖችን የሚያበቅል የፖለቲካ ባሕል መኖሩ ነው ይላሉ። በኢትዮጵያ ላይ ብዙ ጥናት ያደረጉት ጆን ያንግ በዐሥር ዓመታት ልዩነት በኢትዮጵያ የፓርቲ የፖለቲካ ሒደት ላይ በጻፏቸው ሁለት ጽሑፎቻቸው ላይ ለኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካና ዴሞክራሲ ዋነኛ እክል አድርገው የሚያቀርቡት በኢትዮጵያ ያለውን ከመንግሥታዊ መዋቅሩ ውጭ ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ ተቋም እንዲፈጠር ያለመፍቀድ አባዜንና በእርሳቸው ቋንቋ በሃገሪቱ ውስጥ ከ11ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን የቀጠለው ፈላጭ ቆራጭ የፖለቲካ ባሕልን (Authoritarian Political Tradition) ነው። እንደ ጆን ያንግ ሁሉ ዶ/ር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳዩች ላይ አብዝተው የተመራመሩት ጆን አቢኒክና ማሪና ኦታዌ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የትናንት የባሕል ሸክም እንዳጎበጠው እየገለጹ መፍትሔውን ይሄን ባሕል መቀየር ላይ ያደርጋሉ። እንዲሁም ሳራ ቮጋን እና ኬቲል ትሮንቮል የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አወቃቀር፣ ከልጅነት እስከ ዕውቀት ድረስ በተዋረድ (hierarchy) የተሞላ መሆኑ ለዚህ የፖለቲካ ባሕል አለመዳበር እንደመንስኤ ይወስዱታል። “አብዛኞቹ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚኖሩ ዜጎች ተከራክረው፣ ሕይወታቸውን በተሻለ መንገድ ለመዘወር የሚያስችላቸውን አማራጭ ስለመለየት አያስቡም። ሌሎችም ይህንን ያደርጋሉ ብለው አይጠብቁም፤ የበላይ ወይም የበታች ከሚሏቸው ጋር ይህንን ማድረግ ደግሞ ጨርሶ የማይታሰብ ነው” ይላሉ።
ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግን ጨምሮ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በሙሉ በጋራ የሚስማሙበት የሚመስለው ጉዳይ ‹የኢትዮጵ የፖለቲካ ባሕል አለማደግን› ነው። የፖለቲካ ባሕል ሊገለጽ የሚችልባቸው ብዙ መንገዶች ቢኖሩም፣ ‹ጠርዘኝነት› ግን ዋነኛውና ብዙዎቹ የፖለቲካ አመራሮች እንደፈታኝ የሚወስዱት ችግር ነው። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት “የፖለቲካ ባሕላችን ቀኖናዊ ነው” ወይም በሌላ አነጋገር “perfectionist (ፍፁማዊ)… ወይ አርዮስ ወይ ቅዱስ ብሎ የመፈረጅ አባዜ አለበት” የሚሉ ሲሆን፤ አያይዘውም “በእኛ ባሕል የፖለቲካ ሐሳብ ልዩነት ሲኖርህ መጠፋፋት ነው” ይላሉ። ይህ የኢንጅነር ይልቃል ምልከታ ከላይ የጠቀስናቸው ሳራ ቮጋን እና ኬቲል ትሮንቮል ‹The Culture of Power in Contemporary Ethiopian Political Life› በሚል ጥናታቸውን ከደረሱበት ድምዳሜ ጋር የሚስማማ ነው። ምሁራኑ በጥናታቸው ‹መንግሥት እና ተቃዋሚዎች በነገሮች እና ርዕዮተ-ዓለም ጉዳዮች ላይ አይወያዩም። የራሳቸውን ብቻ የፖለቲካ አመለካከት ይዘው እርስ በርስ በመነጋገር ፈንታ፣ አንዱ ሌላውን ይወቅሳል።› አጥኚዎቹ አክለውም፣ ሌላው ቀርቶ በፌዴራል መንግሥቱ ቋንቋ አማርኛ ውስጥ እንደሁለት የተነጣጠሉ አካላት የሚታዩት ‘state’ እና ‘government’ ተነጣጥለው የማይታዩ እና ‹መንግሥት› በሚለው ቃል ብቻ የሚተረጎሙ መሆኑ አንዱ የፖለቲካ ባሕሉ አለማደግ ምልክት አድርገው ይወስዱታል።
የኢ.ዴ.ፓ. የቀድሞው ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው ከፖለቲካ ባሕል አለማደግ ጋር አያይዘው ‹የእኛ የፖለቲካ ባሕል በጦርነትና በመገዳደል ሥልጣን መያዝ ነው፤ የእኛ ፖለቲካ ሲታይ አንዱ ባለኃይል ሌላኛውን ባለኃይል ሥልጣን የሚቀማበት ነው› የሚሉ ሲሆን አያይዘውም “ሕዝብ እንደሚሳሳት ማወቅና እና ሲሳትም ተሳስተሃል ሊባል እንደሚገባው መስማማት ይኖርብናል።” በማለት ባሕሉን እየተቸን ካላሳደግነው የፖለቲካ ሒደቱ የትም አይደርስም የሚል መደምደሚያ ይሰጣሉ።
ነገር ግን ይህ የፖለቲካ ባሕል አለማደግ ነው፣ የፖለቲካችን መሠረታዊ ችግር በሚለው ሐሳብ ሁሉም ምሁራን አይስማሙም። በዚህ ከማይስማሙት ምሁራን አንዱ ቶቢያስ ሐግማን ናቸው። “የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከባሕል አንፃር ብቻ መተርጎም ስህተት ነው” ይላሉ ሐግማን ጆን አቢኒክ ከምርጫ 97 በኋላ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ለጻፉት ጽሑፍ ምላሽ በሰጡበት ጽሑፋቸው። “ከዚህ እይታ ባለፈ ገዥው ፓርቲ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ከውስጡ ምን ያህል የተማከለ እና ፈላጭ ቆራጭ እንደሆነ መረዳቱ ነው ወሳኙ የፖለቲካው ውድቀት መነሻ” የሚሉት ሐግማን “ከዚህ ባለፈ ግን ችግሩን ወደ ባሕል መውሰዱ ገዥውን ቡድን ነጻ ማውጣት ነው የሚሆነው” ብለው የችግሩ መነሻና መድረሻ ገዥው ቡድን እንደሆነ አጽንኦት ይሰጣሉ። ነገር ግን ምሁራኑም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቹ ባሕልን እንደ አንድ የችግሩ ምንጭ እንጅ የችግሩ ብቸኛው መነሻ አድርገው ላለመውሰዳቸው ጽሑፎቻቸውና አስተያየቶቻቸው ይገልጻሉ።

የታጠረው ምኅዳር
የፖለቲካ እሳቤዎች መዝገበ ቃላት እንደሚያስነብቡት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት (multi-party system) ማለት በቁጥር የበዙ እና አሸንፈው መንግሥት በተናጥል ወይም በጥምረት የመመሥረት ዕድል ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ለብሔራዊ ምርጫ የሚሳተፉበት ስርዓት ነው። ሌላው ቀርቶ በእነዚህ ብያኔዎች መሠረት የዴሞክራሲያውያኑ ምዕራብ አገሮች፣ ለምሳሌ የአሜሪካ የፖለቲካ ስርዓት የሁለት-ፓርቲ ስርዓት ነው። በአሜሪካ ከስልሳ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቢኖሩም ከሪፐብሊካን እና ዴሞክራቶች በቀር አሸንፈው መንግሥት ለመመሥረት የሚችሉበት ዕድል ስለሌላቸው (ወይም ዕድላቸው እጅግ ጠባብ ስለሆነ) የአሜሪካ ስርዓት የሁለት-ፓርቲ ስርዓት እንጂ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ሊባል አይችልም።
ከገዢው ፓርቲ ውጪ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል እና አንድ በግል የተመረጡ አባላት ብቻ ከተወከሉበት ምርጫ 2002 ወዲህ ገዢው ፓርቲ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ራሱን ‹አውራ ፓርቲ› በማለት መጥራት ጀምሯል። ይህንኑም ልማታዊ ዴሞክራሲ እያለ ከሚጠራው ከኢኮኖሚ ዕቅዱ ጋር አዋድዶ ለመቀጠል ትልሙ እንዳለው በተለያዩ መድረኮቹ አስታውቋል። ይሁን እንጂ  ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ‘የአውራ ፓርቲ’ (dominant party) ስርዓት እያራመደ ሳይሆን በኢፍትሐዊ መንገድ ያገኘውን የሕዝብ ተወካዮች ወንበር በሕዝባዊ ይሁንታ ያገኘው ለማስመሰል ከመጣሩም ባሻገር ምጣኔሀብታዊ ጠቀሜታ ያለው በማስመሰል ሕዝባዊ ቅቡልነት ለመግዣ እየተጠቀመበት ነው ከሚል ትችት አልዳነም። የአውራ ፓርቲ አካዳሚያዊ ብያኔ ‹አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ተከታታይ ምርጫዎችን በበላይነት ሲያሸንፍ፣ ወደፊትም የመሸነፍ ዕድሉ አነስተኛ ሆኖ ለመገመት የሚያስቸግርበት ስርዓት› እንደሆነ ይደነግጋል። ይህ ዓይነቱ ስርዓት ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የታየው በተለይ በጃፓኑ ዴሞክራቲክ ሊበራል ፓርቲ እና ሌሎች ጥቂት አገራት ብቻ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ የአውራ ፓርቲ ስርዓት የተከሰተባቸው አገራት ታሪክ የሚያሳየው አውራ ፓርቲው ‹አውቶክራት› (ለዴሞክራሲ ያልበቃ፣ በሌላ በኩል የወጣለት አምባገነንም ያልሆነ) ስርዓት ነው።
ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ራሱን አውራ ፓርቲ በማለት መጥራት የጀመረው ፓርቲው ‹ልማታዊ ዴሞክራሲያዊነት በተግባር ተፈትሾ ነጥሮ ወጥቷል› እንዲሁም ምርጫው ‹በኪራይ ሰብሳቢዎች ካምፕ ድንጋጤና ውዥንብር ፈጥሯል› ብሎ በገመገመው ምርጫ 2002 ማግስት ነበር። ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ይሄን ‹አውራ ፓርቲ› የሚል ማዕረግ ለራሱ ሲሰጥ የአውራ ፓርቲ ስርዓት የዘረጉ ዴሞክራሲያዊ አገሮችን ሲዊዲንና ደቡብ ኮሪያ እያለ እያጣቀሰ የአንድ ፓርቲ ስርዓት ሳይሆን ወደ አውራ ፓርቲ ስርዓት እያመራን ነው፤ ይሄም ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ታላቅ እመርታ ነው በማለት ግምገማውን በወቅቱ አስቀምጧል። ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ራሱን አውራ ፓርቲ ብሎ ከመሰየሙ ሦስት ዓመታት ቀደም ብሎ በ1999 የፓርቲዎች የሥነ ምግባር ደንብ ሙሉ ለሙሉ ተገልብጦ መጥቶበታል የተባለው ‹International Institute for Democracy and Electoral Assistance (IDEA)› የአፍሪካ ፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ባቀረበው ሪፖርት ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ከምርጫ 97 ማግስት ወዲህ አውራ ፓርቲ እንደሆነ የሚያትት ነው። ‹IDEA› የአውራ ፓርቲ ስርዓት የሚባለው ስርዓት በአራት መልኩ የዴሞክራሲ ፀር እንደሆነ በሰነዱ ላይ የገለጸ ሲሆን እነዚህም አንደኛ፣ የፉክክር ፖለቲካን ያቀጭጫል፤ ሁለተኛ፣ የሕግ አውጭውን ሥልጣን ጠቅልለው በመያዝ በአንድ አገር ውስጥ ያሉትን ሁሉንም ፍላጎቶች ይቆጣጠራል፤ በሶስተኝነት፣ ጠያቂ ስለማይኖርበት ተጠያቂነት የሌለበት ስርዓት ይፈጥራል እንዲሁም በመጨረሻም፣ የሥልጣን ትዕቢት በመፍጠር ለዜጎች ጥያቄ ደንታ ቢስ መንግሥት እንዲፈጠር ያደርጋል የሚሉ ናቸው። ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. የምርጫ ሥነ ምግባር ሕጉንና የአውራ ፓርቲ ፅንሰ ሐሳብን ከ‹IDEA› ወስዶ ይሄን የድርጅቱን የአውራ ፓርቲ የሰላ ትችት እንዳላየ ሁኖ በማለፍ በተለያዩ የፓርቲው ሰነዶች አሁንም አውራ ፓርቲ መሆኑን እየገለጸ ይገኛል።
የኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ወዳጅ እንደሆኑ የሚነገርላቸው ታላቁ ሊቅ ሳሙኤል ሀንቲንግተን ‹ዴሞክራሲ ሊጠናከር የሚችለው መንግሥት በምርጫ ሥልጣን ሊያጣ ሲችልና ሥልጣን ላይ የወጣው አዲስ ፓርቲም እንዲሁ ሥልጣኑን በምርጫ ሊያጣ ሲችል ብቻ ነው› በማለት የሥልጣን ሽግግር የዴሞክራሲ ምሰሶ መሆኑን ያስረዳሉ። ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. የወዳጆቹንም የጠላቶቹንም ምክር ወደ ጎን ብሎ የት እንደሚያደርሰው ባይታወቅም አሁንም የፖለቲካ ሥልጣኑን ሙሉ ለሙሉ ጠቅልሎ ይዞ ይገኛል።
አሁን አሁን ደግሞ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ራሱን የሚጠራበት ‹አውራ ፓርቲ› የሚለው ስያሜ የሚያንሰው እንደሆነ ተቺዎች መናገር ጀምረዋል። አንዳንዶች አሁን ፓርቲው ከመሠረቱ ሲያራምደው ከነበረው ሶሻሊስታዊ የብዝኃ አደረጃጀት (Mass Party) ቅርፅ ላይ የመንግሥታዊ ፓርቲነት (Cartel Party) ካባ ደርቦ ወፍሯል የሚለው ትችት ለዚህ አንዱ ማሳያ ነው። መንግሥታዊ ፓርቲዎች የመንግሥትን ሀብት እንደፈለጉ የሚጠቀሙ ፓርቲዎች ሲሆኑ፤ አንዳንዴ የፓርቲና የመንግሥት መዋቅሮችን መለየት እስኪያስቸግር ድረስ አንድ ላይ የሚያዋህድ ቅርፅ ነው። ከዚህ መንግሥትና ፓርቲን ካልለየ አካሄድ ጋር ተያይዞ “ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ” የጣሊያናዊውን ማውሮ ሴሊዜን (Mauro Calise) ቋንቋ በመዋስ “ወደ ፓርቲክራሲ (Particracy) ቀይሮታል” ወደሚል መደምደሚያ ላይ እየደረሱ የሚገኙ ብዙዎች ናቸው።
በዚህ የኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. የመጠቅለል አካሄድ ላይ ስጋት የገባቸው የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢ.ዴ.ፓ.) የቀድሞ ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው “ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. በይዘት ከቻይና አስተሳሰብ ብዙም አይለይም” ይላሉ። የቻይና አስተሳሰብ የሚሉት፣ ‹አሁን ባለንበት ሁኔታ ዴሞክራሲ አያስፈልገንም፣ የሚያስፈልገን የኢኮኖሚ ሪፎርም ነው› የሚለውን ነው። የቻይና መንግሥት ይህንን የሚያደርገው በይፋ የአንድ ፓርቲ የፖለቲካ ፓርቲን ደንግጎ ነው። በቻይና ሕጋዊ ዕውቅና ያለው አንድ ‹የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ› ብቻ ነው። የቻይና የፖለቲካ ስርዓት አሀዳዊ እንጂ አውራ ፓርቲ ስርዓት አይባልም። ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ግን ይህንን ማድረግ ያልቻለው፣ ደርግን ጥሎ አዲስ አበባ እግሩ በረገጠበት ሰዓት የቀዝቃዛው ጦርነት እየከሰመ ዓለም በሁለት ‹ብሎክ› የሚጠራበት ስርዓት እያበቃ በአንድ ዓለምዐቀፍ አስተሳሰብ እየተጠራ ስለነበር “የቻይና አካሔድ የሚበጅ ሆኖ ባለማግኘቱ” እንደሆነ አቶ ልደቱ ይናገራሉ። ስለሆነም “በወረቀት የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ደንግጎ፣ በተግባር ግን የቻይናን መንገድ ይከተላል”።
እንደ አቶ ልደቱ ገለጻ “ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ያስፈልገዋል ብሎ አያምንም። ለዚህ ሕዝብ አሁን ዴሞክራሲ አያስፈልገውም… የዳቦ ጥያቄው ከተመለሰ በኋላ ይደርስበታል ብሎ ነው የሚያምነው።”
የኦሮሞ ፌዴራል ኮንግረስ (ኦ.ፌ.ኮ.) ሊቀመንበር እና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ዶ/ር መረራ ጉዲናም ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. የመድብለ ፓርቲን የሚያስተናግድ አስተሳሰብ እንደሌለው ይናገራሉ። “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” ይላሉ ዶ/ር መረራ “የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለማስተናገድ የተፈጠረ አይደለም”። በኢትዮጵያ መድብለ ስርዓትን የሚፈቅድ “የይስሙላ ጨዋታ” የተፈቀደው ዕርዳታ ለጋሽ አገራትን ለማስደሰት ብቻ ነው” በሚል ነው ዶ/ር መረራ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት አለ ሊባል የሚችለው ብለው የሚያስቡት።
የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲው የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ዶ/ር ካሳሁን ብርሃኑ የኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን የመጀምሪያ የሥልጣን ዘመናት በገመገሙበት ጽሑፋቸው ይሄን አካሄድ የኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. የአግላይነት ፖለቲካ (politics of exclusion) ያሉት ሲሆን፤ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ያልተመቸውን ሰውም ሆነ ድርጅት ወደ ጎን እየገፋ ዙሪያውን በራሱ ሰዎች መክበብን እንደ ዋነኛ የሥልጣን ላይ መቆያ ዘዴ እንዳደረገው አያይዘውም ይገልጻሉ። ዶ/ር ካሳሁን ይህን ካሉ ከ15 ዓመታት በኋላ ይህ አካሄድ መባስ እንጅ መሻሻልን እያወቀ አይደለም።

የተበላሸ ዘርና ተጣሞ ‘ያደገ’ ተክል
የፓርቲ ፖለቲካ ላይ የሚቀርበው ሌላው መሠረታዊ ትችት የፖለቲካው ተዋንያንንና ከተዋንያኑ አደረጃጀት ጋር ተያይዞ የሚቀርብ ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያቋቁሟቸው ግለሰቦች በራሳቸው ብዙ የራሳቸው የግል ፍላጎት ያሏቸውና ተደራጅተው ከሌሎች ጋር መሥራት የሚቸግራቸው ናቸው ከሚለው ሐሳብ ነው ትችቱ የሚጀምረው። ዶ/ር ወንድወሰን ተሾመ በአሁኑ ወቅት ያሉ የኢትዮጵያ ፓርቲ ፖለቲካ ተዋንያንን በሰባት መደቦች ያስቀምጧቸዋል። በዐፄ ኃይለሥላሴ ስርዓት አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ (ex-minsters of the ancien régime)፣ የግራ ፖለቲከኞች (leftists)፣ የቀድሞ የግራ ፖለቲከኞች (ex-leftists)፣ ፋኖ ያሉ ፓርቲዎች (rebels)፣ ታማኝ ተቃዋሚዎች (loyal oppositions)፣ አስመሳይ ተቃዋሚዎች (phony oppositions) እና በፊት ኢሕአዴግ ውስጥ የነበሩ (ex-EPRDF members) በማለት። እንግዲህ እነዚህ በተለያዩ የዕድሜ ክልሎች ላይ ያሉ ተዋናዮች (አንዳንድ ከሁለት በላይ ባሉ መደቦች ውስጥ እየገቡ) የራሳቸውን ፍላጎት ለማራመድ ሲሉ ሌሎችን እየጠለፉ ሁሉም የፖለቲካው ከፍታ ላይ መድረስ እንዳይችሉ ሁኗል።

የኢትዮጵያ የፖለቲካ የውስጥ ፓርቲ የዴሞክራሲያዊነት (intra-party democracy) ችግር እንዲሁም ተቋማዊ ቁመና (Institutionalization ) የመያዝ ችግር አለባቸው የሚለው ትችትም ሁሌም የሚሰማ ነው። ሮበርት ሚሸልስ የተባሉ ምሁር የውስጥ ፓርቲ ዴሞክራሲን ይዞ የተደራጀ መዋቅር ያለውና ተቋማዊ ቁመና ያለው ፓርቲ ማቋቋም አብረው ሊሄዱ የማይችሉ (inconsistent) ጉዳዩች ናቸው ይላሉ። ፓርቲን ተቋማዊ ቅርፅ አስይዞ በተመሰሳይ ወቅት ዴሞክራሲያዊ ላድርግ ማለት የኋላ ኋላ ሁለቱንም ያሳጣል የሚል ነው የሐሳቡ አንኳር። ኢንጅነር ይልቃል በዚህ ሐሳብ የሚስማሙ ይመስላሉ። እርሳቸው እንደሚሉት ‹የፓርቲ አባላትን ዲስፕሊንድ አድርጌ የውስጥ ፓርቲን ዴሞክራሲ አሰፍናለሁ ማለት በዚህ ዘመን ከባድ ነው› ይላሉ። አያይዘውም የውስጥ ዴሞክራሲን በፓርቲ ውስጥ አስፍኖ የፓርቲ ዲሲፕሊን የሚባለውን ጉዳይ ወደ ጎን  ብሎ የንቅናቄ ቅርፅ ያለው ፓርቲ ይዞ መቀጠልን እንደሚመርጡ ይገልጻሉ።
የተቃዋሚ ፓርቲዎቹ አሉባቸው ከተባሉት የአባላት ችግር እና የውስጠ ፓርቲ ቁመና ችግር ባለፈ ያለምንም ዓላማ አዳዲስ ፓርቲዎች እየተቋቋሙ እርስ በርሳቸው ይጠላለፋሉ የሚል ትችት ይቀርብባቸዋል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ድረ-ገጽ ላይ (ሚያዝያ 28/2008 እንዳየነው) የተዘረዘሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች 75 ናቸው። ከ2007 ምርጫ በፊት ‹ለቀጣዩ ምርጫ በንቃት የሚሳተፉ ፓርቲዎች ዝርዝር› በሚለው ስር የተዘረዘሩት ፓርቲዎች ቁጥር ግን ጠቅላላ ከተባለው የፓርቲዎች ዝርዝር ይበልጣል። እሱም በእንግሊዝኛው እና በአማርኛው ላይ የተለያየ ሁኖ እናገኘዋለን። በእንግሊዝኛው 79 ሲሆኑ፣ በአማርኛው 76 ናቸው። ከዚህ የቁጥር ዝብርቅርቅ በተቃራኒው፣ ብዙዎች የሚተቹት ብዛታቸው እና የርዕዮተ-ዓለም ልዩነታቸው የማይጣጣም መሆኑን ነው። ምንም እንኳን ብዙዎቹ ፓርቲዎች በዘውግ ከመደራጀታቸው በቀር ልዩነት ባይኖራቸውም መንግሥት ለመመሥረት በሚያስችላቸው ቁመና ለመቆም ጥምረት ወይም ግንባር ሲፈጥሩ አይታዩም። ኅብረ-ብሔራዊ መሠረት ይዘው የተደራጁትም፣ ግልጽ የሆነ የርዕዮተ-ዓለም ልዩነት ባይኖራቸውም ተደራጅተው ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን ለመገዳደር በሚያስችላቸው መዋቅር ለመቅረብ አልሞከሩም፣ ቢሞክሩም አልተሳካለቸውም።
ዶ/ር መረራ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥር መብዛት ችግር ነው ብለው አያምኑም። “እስራኤል 5 ሚሊዮን ሕዝብ ብቻ ነው ያላት፤ ነገር ግን ከ30 በላይ በአገሪቱ ሕልውና የማይደራደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ስለዚህ ለ100 ሚሊዮን ሕዝብ ብዙ ፓርቲዎቹ ቢኖርም ያን ያክል ችግር አይደለም። ችግሩ፣ እነዚህ ፓርቲዎች ለሕዝብ ጥቅም የቆሙ ናቸው ወይስ አይደሉም፤ ለራሳቸውም ሥልጣን ለማግኘት ቢሆን ችግር የለውም፤ እንዲሁ የገዢው ፓርቲ ቀለብ የሚሰፍርላቸው ናቸው የሚለው ነው የሚያሳስበው” ይላሉ። የሌሎች አገራትን ተሞክሮ ስንመለከትም ዶ/ር መረራ ከሚሉት እውነታ ብዙም የራቀ ድምዳሜ ላይ አንደርስም። ኬኒያ በአንድ ወቅት እስከ 160 የሚደርሱ የተመዘገቡ ፓርቲዎች ነበሯት፤ ናይጄሪያም 60 የሚሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ደቡብ አፍሪካንም የወሰድን እንደሆን ከ80 በላይ ፓርቲዎች ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱባት ሀገር ነች። ከዚህም አንፃር ኢትዮጵያ ውስጥ የፓርቲዎች መብዛት መሠረታዊ ችግር ነው የሚለው ሐሳብ ትክክል ነው ማለት አይቻልም። መሠረታዊው ችግር ያለው ‹እነዚህ ፓርቲዎች እንቅስቃሴያቸው ምን ይመስላል? የፓርላማ ውክልናቸውስ?› የሚለው ነው የሚሆነው። ኬኒያ ካሏት ፓርቲዎች መካከል 23 የሚሆኑት የፓርላማ ውክልና አላቸው፤ በናይጀሪያም 6 ፓርቲዎች በፓርላማ መቀመጫ ያለቸው ሲሆን፤ ደቡብ አፍሪካ ደግሞ 13 በፓርላማ ወንበር ያላቸው የፓርላማ ፓርቲዎች (Parliamentary Parties) አሏት። እንግዲህ የኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ አሳዛኝና አሳሳቢ የሚሆነውም ከዚህ አንጻር ስንመለከተው ነው። በአሁኑ ወቅት ገዥው ፓርቲ ብቻ በፓርላማ ተወክሎ የፈለገውን የሚወስንበት ጊዜ ሲሆን፤ ይሄም የፓርቲ ፖለቲካ የሚባለውን ሐሳብ ሙሉ ለሙሉ እንዳይቀብረው የብዙዎች ስጋት ነው።
ዶ/ር መረራ በኢትዮጵያ ‹የፈሉትን› የፖለቲካ ፓርቲዎች “አንዳንዶቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከራሳቸው [ከሊቀመንበሮቹ] የግል ዝና ያለፈ ቁመና ያላቸው አይመስለኝም…” ሲሉ አቶ ግርማ ሰይፉ ደግሞ “በአንድ ሰው የሚዘወሩ ሱቆች ወይም ከሱቅ በላይ ማዕረግ የሌላቸው ናቸው” ይሏቸዋል። አቶ ግርማ የሚያስገርማቸው “አንደኛ፣ እንደዚህ ዓይነት ፓርቲዎች እንዲቋቋሙ የሚፈቅድ መንግሥት መኖሩ እና ፓርቲዎቹ ውስጥ ለመሰባሰብ የሚፈቅዱ አባላት መኖራቸው” ነው። አቶ ግርማ፣ ሲቪክ ማኅበራት ሲዋቀሩ ብዙ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያስቀምጥ መንግሥት፣ አገር እንመራለን ብለው የሚደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ‹በነጻ የመደራጀት መብትን ለማክበር› በሚል ሰበብ ብቻ እንዲሁ መተው ተገቢ እንዳልሆኑ ይናገራሉ። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ፕ/ር መርጋ በቃና በሕዳር ወር 2007 በሰጡት ይፋ ቃለ ምልልስ “75 [የፖለቲካ ፓርቲዎች] አሉ። ነገር ግን የሕግ ጉዳይ ያላሟሉና ሥልጣንን ሞኖፖላይዝ ያደረጉ እንዲሁም ራሳቸው ባወጡት ደንብ መሠረት ለ18 ዓመታት ጠቅላላ ጉባኤ ያልጠሩ አንዳንድ ፓርቲዎች ይገኙበታል። ለዴሞክራሲው ስንል በሆደ ሰፊነት ነው የምንይዛቸው” ብለው ነበር። አመራር የነበሩበት አንድነት ፓርቲ በእርሳቸው አገላለጽ ‹ፍትሐዊ ባልሆነ መንገድ› በምርጫ ቦርድ ጣልቃ ገብነት የተሰነጠቀባቸው እና ለሌሎች ተላልፎ የተሰጠባቸው አቶ ግርማ ሰይፉ ግን ይህ አባባል አይዋጥላቸውም። “ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. እንዲህ ዓይነቶቹን ‹ሱቅ› የፖለቲካ ፓርቲዎች ዝም የሚላቸው ለሥልጣኑ ስለማያሰጉት እና ስለሚፈልጋቸው ነው።” በማለት ነው ሐሳባቸው የሚገልጹት።
አቶ ልደቱ አያሌው “ኢትዮጵያ ውስጥ በሕግ የተመዘገበ፣ ሰርቲፊኬት ያለው ተቃዋሚ ፓርቲ እንጂ በተግባር ግን ለኢትዮጵያ ሕዝብ የትግል እንቅስቃሴ የሚመጥን ተቃዋሚ ፓርቲ እስካሁን አልተፈጠረም። በምርጫ ቦርድ መስፈርቱን አዘጋጅተን ተመዝግበናል። ሕጋዊ ፈቃድ አለን፣ ቢሮ አለን፣ እንንቀሳቀሳለን። ምርጫ እንወዳደራለን። አሁን ካለው የኢትዮጵያ ሁኔታ አንፃር ግን፣ በተለይ የኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን ዓይነት ግዙፍ ድርጅት ተቋቁሞ ለሥልጣን መብቃት የሚችል የፖለቲካ ፓርቲ እስካሁንም አልተፈጠረም፤ አሁንም የለም።” በማለት አቶ ግርማ ‹ሱቅ› እያሉ የሚጠሯቸው ብቻ ሳይሆኑ ሌሎቹም ፓርቲዎች ሕዝቡን በሚመጥን ቁመና ላይ እንደሌሉ ይሟገታሉ። አቶ ልደቱ ለዚህ ችግር መንስኤ ናቸው የሚሏቸውን አምስት ነጥቦች ዘርዝረዋል። “አንደኛ፣ ፖለቲካችን የሐሳብ ፖለቲካ አልሆነም፤ ሁለተኛ፣ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ሚና መጫወት የሚችለው የኅብረተሰብ ክፍል በተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥ ተሳትፎ አያደርግም፤ ሦስተኛ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ውስጣዊ ዴሞክራሲ የላቸውም፤ አራተኛ፣ አካባቢያዊ ስሜት በፓርቲዎች ውስጥ ነግሷል፤ አምስተኛ፣ ፓርቲዎቹ የውጪ ፖለቲከኞች ላይ ጥገኛ ናቸው” በማለት ያስቀምጧቸዋል።
የኢትዮጵያ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥራቸው ቢበዛም በአሁኑ ወቅት አንድም የፓርላማ ወንበር መያዝ አልቻሉም። ከላይ ካነሳናቸው የውጭና የውስጥ ችግሮች በተጨማሪ ከውሕደትና ጥምረት ጋር ተያይዘው የሚቀርቡባቸው ትችቶችም አሉ። ትችቱ ተዋሃዱ የሚል ብቻ ሳይሆን ለመዋሃድ ሲባል ፓርቲዎች መሠረታቸውን እየናዱ ይፈርሳሉ፤ መዋሃድን እንደ ግብ መውሰዳቸው ስህተት ነው የሚልም ነው። በዚህም መሠረት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ ከሁሉም ፈታኝ የሆነ ችግር እንደሆነ ብዙዎች የሚስማሙበት መተባበር አለመቻልን ነው። መተባበሩ ቀርቶ አንድ ፓርቲ ሳይሰነጠቅ እየጎለበተ መሄድ የሚችልበት ሁኔታም በተቃውሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ የሚናፈቅ ነገር ሆኗል የሚሉም አልታጡም። በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስ ምሁሩ አቶ አስናቀ ከፋሌ ‹The (un)making of opposition coalitions and the challenge of democratization in Ethiopia, 1991–2011› በሚል ርዕስ ባሳተሙት ጥናታቸው ላይ ምርጫ 97 ላይ የመተባበር (coalition) ፖለቲካ እመርታ ታይቶ እንደነበር ይገልጻሉ። በዚህም ተቃዋሚዎች ‹ለምርጫ ሕጎች መሻሻል እና በአካባቢያዊ እና ብሔራዊ ደረጃ ጉልህ ውክልናን ለማሸነፍ በሚያስችል ሁኔታ መደራደር ቢችሉም፣ ያንን ማስቀጠል አልቻሉም። ያኔ እና ከዚያ በኋላ ትብብሮች ውጤታማ ሊሆኑ አልቻሉም› ብለዋል።
አቶ አስናቀ በዚሁ ጥናታቸው፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ትብብር አለመሳካት መንስኤ ሆነዋል የሚሏቸውን ሰባት ምክንያቶች በጽሑፋቸው ላይ ዘርዝረዋል። 1ኛ፣ ከልካዩ የፖለቲካ ምኅዳር እና የመንግሥት ተፅዕኖ፤ 2ኛ፣ በርዕዮተ-ዓለማዊ መግባባት ሳይሆን በሥመ-ተቃዋሚነት ብቻ ለመተባባር መስማማት፤ 3ኛ፣ የዳያስፖራ ፖለቲከኞች በተለያዩ ቡድኖች የመቧደን ተፅዕኖ፤ 4ኛ፣ የጋራ መግባቢያ የመፍጠር ልምድ ማነስ እና የዴሞክራሲ ባሕል እጦት፤ 5ኛ፣ የድርጅት ነጻነት (independence) ከግምት ውስጥ ያላስገባ ‹ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ› በሚለው ግፊት ብቻ የማይዘልቅ ጥምረት መመሥረት፤ 6ኛ፣ በተጣማሪዎቹ ድርጅቶች መካከል ያለ የኃይል/ሥልጣን ሽሚያ፤ እና 7ኛ፣ በተጣማሪ ቡድኖች መካከል መተማመን አለመኖር ለብዙዎቹ ጥምረቶች ስኬት ማጣት እና መልሶ መፍረስ ሰበቦች መሆናቸውን አመላክተዋል።
ከዚህ ከአቶ አስናቀ ትችት በተመሳሳይ አቶ ልደቱ አያሌው ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ችግሮች ‹አንዱ መተባበርን እንደግዴታ የሚወስድ ባሕል መኖሩ እንደሆነ ይናገራሉ። የተለያየ የፖለቲካ ግብ ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን ለመገዳደር ብቻ ሲባል እንዲተባበሩ ግፊት ይደረግባቸዋል። የሚተባበሩት በርዕዮተ-ዓለም አንድ ሆነው ስላይደለ ኅብረታቸው አይሰምርም› ይላሉ። ማኅበር (ወይም የፖለቲካ ድርጅት) መመሥረት በራሱ መተባበር እንደሚጠይቅ የሚናገሩት ኢ/ር ይልቃል ደግሞ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል “የመተባበር አስፈላጊነት ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ነገር አይደለም” ባይ ናቸው። ይልቁንም፣ ኢንጅነር ይልቃል እንደችግር የሚወስዱት ያላደገው የፖለቲካ ባሕላችን ችኩልነትን እና ፍፁማዊነትን መሻቱን ነው። ማኅበሮች በችኮላ እንዲመሠረቱ እና ፍፁማዊ ስኬት እንዲያስመዘግቡ ይጠበቃል። ይህ ደግሞ አይሳካም ይላሉ። “አለመተባበርም፣ ለውጤት የመጓጓትም ችግሮቹ አንድ ናቸው፤ ምንጩን ስናየው ውጤቱን በአንድ ሌሊት ለማየት መጓጓት ነው። ቅንጅትንም ያፈረሰው ይሄው ነው” ብለዋል።
በመጨረሻም ፓርቲዎች ውጤት ለማምጣት ላለመቻላቸው የሚጠቀሰው ምክንያት የአደረጃጀታቸው ጉዳይ ነው። ይሄም ሕብረ-ብሔራዊና የዘውግ (ethnicity) አደረጃጀት የሚለው ክፍፍል ኅብረ-ብሔራዊ የሚባሉት ፓርቲዎች ጎልተው እንዳይወጡ አድርጓቸዋል፤ የብሔር መሠረት ያላቸው ፓርቲዎች ደግሞ ከራሳቸው ማዕቀፍ ወጥተው ጠንካራ ተገዳዳሪ መሆን እንዳይችሉ አደረጃጀታቸው በራሱ ያግዳቸዋል የሚለው ነው።
በ1960ዎቹ በጋናዊው ኩዋሚ ኑኩሩማህ ጀማሪነት የተጀመረው የአፍሪካ ፓርቲዎችን በንዑስ መሠረት (particularistic) ላይ እንዳይመሠረቱ መከልከል እየተለመደ መጥቶ ከ1990ዎቹ ወዲህ እጅግ ሰፍቶ በአሁኑ ወቅት ከኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ውጭ ፓርቲዎች ዘውግንም ሆነ ሃይማኖትን መሠረት አድርገው የተደራጁበት የሰሃራ በታች የሚገኝ የአፍሪካ ሀገር አለ ማለት አይቻልም። አብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገራት ፓርቲዎች ዘውግን መሠረት አድርገው የሚደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሕግ የተከለከሉ ናቸው። ለዚህም የሚሰጠው ዋነኛ ምክንያት እንደዚህ ያሉ አደረጃጀቶች ከፋፋይና (divisive) የሲቪል የፖለቲካ ሂደት እክል ናቸው የሚል ነው። ወደ ኢትዮጵያ ስንመጣ ከላይ ባየነው የአፍሪካ እውነታ በተቃራኒው በአሁኑ ወቅት ገዥውን ግንባር ጨምሮ አብዛኞቹ ሕጋዊ ዕውቅና ያላቸው ፓርቲዎች የአደረጃጀት መሠረታቸው ዘውግ ነው።
ከዚህ መሬት ላይ ያለ እውነታም በመነሳት ‹በአሁኑ ወቅት በተሻለ የጥንካሬ ቁመና ላይ የሚገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች በብሔር ወይም በዘውግ የተደራጁት ናቸው፤ ኅብረ-ብሔራውያኑ ተዳክመዋል። ኅብረ-ብሔራውያኑ ፓርቲዎች የመሰነጣጠቅ አደጋ የሚያንዣብብባቸው በውስጣቸው በዘውግ የመቧደን አባዜ ስለሚከሰት ነው› በማለት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ የሚከሰቱ ውስጣዊ መዳከሞች እና መከፋፈሎች ላይ መንስኤው በዘውግ መደራጀት መፈቀዱ ነው የሚሉ ፖለቲከኞች ጥቂት አይደሉም። በአፍሪካ ውስጥ (ኬንያ እና ጋናን ጨምሮ) በዴሞክራሲ እያበቡ ያሉ አገራት በዘውግ መደራጀትን በይፋ በማገዳቸው የመድብለ ፓርቲ ስርዓታቸው ፈተና ውስጥ እንዳልወደቀ የሚከራከሩ አሉ።
አቶ ልደቱ አያሌውም ፖለቲካችን በከፍተኛ ሁኔታ የብሔር ፖለቲካ ያጠላበት መሆኑን አምነው፤ እንደሌሎች የአፍሪካ አገራት በዘውግ መደራጀትን ማገድ ያስፈልግ ይሆን ወይ ለሚለው ጥያቄ “የብሔር ፖለቲካን በሕግ ማገድ ያስፈልጋል ባልልም፣ እንደማይጠቅም ግን አምናለሁ” ይላሉ።
በሌላ በኩል በዘውግ የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ‹ኅብረ-ብሔራዊ የሚባል ፓርቲ የለም። ኅብረ-ብሔራዊ ነን ብለው የሚደራጁት የአንድ ብሔር ሰዎች እና የከተማ ሰዎች ብቻ ናቸው› ብለው በተቃራኒው ይከራከራሉ። ባለፈው የፓርላማ ዘመን በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ እና የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አመራር አባል የነበሩት አቶ ግርማ ሰይፉ ይህንን አስመልክቶ “አንድነት ፓርቲ የሁሉም ቤት ይሁን ብለን ስንሠራ ትልቁ ተግዳሮት የሆነብን ብሔር ተኮር የሆነው አመለካከት የሚጎትታቸው ብዙ ሰዎች መኖራቸው ነው። ለምሳሌ አንዳንድ አባላት የብሔር ፖለቲካ ታማኝነታችን መድረክ [አሁን የብሔር ድርጅቶች ብቻ ስብስብ] ውስጥ በመቆየት የሚገለጽ የሚመስላቸው አሉ። አንድነት ፓርቲ ውስጥ አባል ሆነው የሚቆዩት ፓርቲው የመድረክ አባል ሆኖ እስከ ቆየ ድረስ እንደሆነ ቅድመ ሁኔታ አድርገው የሚያስቀምጡ አሉ። ኅብረ-ብሔር ነኝ ብሎ ተደራጅቶ ውስጣዊ ፍልስፍናው ዘውጋዊ የሚሆንበትም ጊዜ አለ” ብለዋል።
አቶ ልደቱ የአንድ ብሔር ሰዎች አንድ ድርጅት ውስጥ በዝተው ስለታዩ ፓርቲው ኅብረ-ብሔራዊ አይደለም አያሰኘውም። ይልቁንም “ፓርቲው የተደራጀበት አስተሳሰብ ነው ድርጅቱ ኅብረ-ብሔራዊ ነው አይደለም የሚለውን የሚወስነው” ይላሉ። ለምሳሌ ‹ኢዴፓ 46 በመቶ የሚሆኑት አባላቱ የደቡብ አካባቢ ሰዎች ናቸው› በማለት፣ ከአስተሳሰባቸው በተጨማሪ ኅብረ-ብሔራውያን ነን የሚሉት የአንድ አካባቢ ሰዎች ናቸው የሚባለው ሁሉ እውነት እንዳልሆነ ይከራከራሉ። አቶ ልደቱ “በተጨማሪም፣ አንዳንድ ጊዜ የመረጃ እጥረት ያለ ይመስለኛል” ይላሉ። “ተቃዋሚ ፓርቲዎች ውስጥ ጠንካራዎቹ እነማን ናቸው የሚለው ላይ እስካሁን ድረስ በተካሄዱት ምርጫዎች ላይ የተገኙትን ድምፆች መለስ ብለን ብናየው፣ ብዙ ድምፅ ያገኙት የብሔር ድርጅቶች ሳይሆኑ ኅብረ-ብሔር ድርጅቶች ናቸው” ይላሉ።
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ከዚህ የተለየ አመለካከት ነው ያላቸው። ኢ/ር ይልቃል “ኅብረ-ብሔራዊ” በሚለው አላምንም ይላሉ። እንደእርሳቸው ሰማያዊ ፓርቲ ራሱን “ኅብረ-ብሔራዊ” ብሎ አይጠራም። “ምናልባት አንዳርጋቸው ጽጌ በሚጠቀምበት አማርኛ ‹ዘውግ-ዘለል› ብንለው ይሻል እንደሆን አላውቅም፤ ፓርቲዎች ወይ የዘውግ ፓርቲዎች ናቸው አለበለዚያ ደግሞ የርዕዮት-ዓለም ፓርቲዎች ናቸው ማለት ነው። በሐሳብ ደረጃ በዜግነት ላይ የተመሠረቱ ፓርቲዎች አሉ፤ አለበለዚያ ‹ኅብረ-ብሔር› የሚለው ቃል ራሱ የመጣው የአንድ ብሔር አደለንም ለማለት ነው እንጂ ዘውግን መሠረት አላደረጉም ማለት አይደለም” ይላሉ። ይሁን እንጂ ኢ/ር ይልቃል የዘውግ አደረጃጀት በቅርብ የሚያስተሳስሩ የወል ሥነ-ልቦና ስለሚኖሩት በፍጥነት የተወሰነ ጊዜ መዝለቅ የሚችል ድርጅት ለመፍጠር እንደሚጠቅምም አበክረው ይናገራሉ። ‹ዘውግ-ዘለል› የሆነ ተቋም ለመመሥረት ግን ጊዜ ስለሚወስድ በመሐል ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ም በቀላሉ መስበር የሚችልበት ዕድል ይኖረዋል፤ ሌሎችም ሁኔታዎች ይፈታተኑታል በማለት በርዕዮት-ዓለም የሚደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዘውግ ከሚደራጁት ይልቅ ከፍተኛ ተግዳሮት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
አቶ ግርማ ሰይፉ በዘውግ መደራጀት “ግብ የለውም” ብለው ነው የሚያምኑት። “ሌላው ቀርቶ ብዙ ሕዝብ ያለው የኦሮሚያ ክልል ነው። ኦሮሚያ ክልልን መሠረት አድርገው የተደራጁት እንኳን አገር የማስተዳደር ግብ የላቸውም። ክልል ማስተዳደርን ግብ ሊያደርጉ ይችላሉ፤ ይህ ግን ሰንካላ ግብ ነው። አገር የማስተዳደር ግብ ሊኖራቸው አይችልም። አገር ለመምራት ከፈለጉ ሌላ አንድ ድርጅት መፈለግ አለባቸው። አንድ ፓርቲ ሲቋቋም በራሱ መንግሥት ለመመሥረት እንዲችል ሆኖ መሆን አለበት።” በማለት መንግሥት ለመመሥረት ከሚያስችል ባነሰ አደረጃጀት የሚቋቋሙ ድርጅቶች ግብ የላቸውም በማለት አምርረው ይተቻሉ። “በደቡብ ክልል አንዳንዶች አንድ የፌዴራል ምክር ቤት መቀመጫ የሚያስገኝ የዘውግ አደረጃጀት ይዋቀራሉ፤” የሚሉት አቶ ግርማ “እነዚህኞቹ ድርጅቶች በክልል ምክር ቤትም ይሁን በፌዴራል ደረጃ ምንም ፋይዳ የላቸውም። ግብ የላቸውም” ብለዋል።
ዶ/ር መረራ ጉዲና በዚህ ዘውጋዊ አደረጃጀትን የማይቀበል አካሄድ አይስማሙም። “[በዘውግ መደራጀት በሌሎቹ አገራት] በሕግ ባይፈቀድም በተግባር ግን አለ፤ ኬንያን ለምሳሌ ብትወስድ ኪኩዩ ካልሆንክ ለፕሬዚዳንትነት ተወዳድረህ ማሸነፍ ያስቸግርሃል።… ለምሳሌ ኦዲንጋ እና ኡሁሩ ኬንያታ በምንም አይገናኙም። ኦዲንጋ በልምድም በዕውቀትም ይበልጠዋል። ኡሁሩ ያሸነፈው ኪኩዩ ስለሆነ ነው። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ዙማ ፕሬዚዳንት የሆነው ዙሉ ስለሆነ ነው እንጂ በመደበኛ ትምህርት እንኳን አልዘለቀም። እኔ የአፍሪካ ፖለቲካን እስካነበብኩ ድረስ ታንዛንያውያን ብቻ ነው ይሄ ነገር የሌለባቸው። እነሱም [የዘውግ] ቡድኖቻቸው ትንንሽ በመሆናቸው ነው። ይሄ ነገር የሚቀንሰው ካፒታሊስቶቹ ጋር ነው። እነሱ የሚደራጁት በጥቅም ፍልስፍና ነው። ነገር ግን በዘር መቧደን እዛም ይቀራል ማለት አይደለም። ለምሳሌ ጥቁር አሜሪካውያን 80 በመቶ ኦባማን ሲመርጡ እንደነበር ይታወቃል” ይላሉ። አያይዘውም አንድ ፓርቲ ኅብረ-ብሔራዊ ነኝ ስላለ ብቻ የብሔር መሠረት የለውም ማለት አይደለም በማለት መከልከሉ ምንም ዓይነት ውጤት ያመጣል ብለው እንደማያስቡ ይገልጻሉ።
ነገሩ መነሳቱ በአደረጃጀት ደረጃ ያለውን ግንዛቤ ያጠራዋል በሚል ሐሳብ እንጅ ገዥው ፓርቲ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ራሱ በዘውግ የተደራጀ ፓርቲ ሆኖና ሕግ የማውጣቱን ሒደትና መሣሪያ ሙሉ ለሙሉ ተቆጣትሮት ባለበት ሁኔታ የራሱን አደረጃጃች ሕገ ወጥ የሚያደርግ መመሪያ ያወጣል ብለን ማሰብ ቅዥት ነው የሚሆነው።

ቻው ቻው የፓርቲ ፖለቲካ?
አሁን አሁን በኢትዮጵያ የሠላማዊ የፖለቲካ መድረክ ላይ ለብዙ ዓመታት ተዋናይ የነበሩ ግለሰቦችን ጨምሮ በብዙዎች ዘንድ የፓርቲ ፖለቲካን በአሁኗ ኢትዮጵያ ማካሄድ አይቻልም የሚል ድምዳሜ ላይ ሲደርሱ ይታያል። ከእነዚህ የፓርቲ ፖለቲካ ተስፋ ከቆረጡ ግለሰቦች መካከል አቶ ግርማ ሰይፉ አንዱ ናቸው። አቶ ግርማ ‹ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን የሚያክል የሠላማዊ ትግል እክል ባለበት አገር ተቃዋሚዎችን ለመውቀስ የሞራል ብቃቱ የለኝም› ይላሉ። ለአቶ ግርማ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. በኢትዮጵያ ተወልዶ የነበረውን የፖለቲካ ፓርቲ ትግል ወደ መቃብር ሸኝቶታል የሚል እምነት አላቸው። ከዚህ በኋላ በፓርቲ ቁመና ተደራጅቶ ልታገል ማለት ተደራጅቶ ለኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. መመቸትና ለመጥፋት መንደርደርም ነው ብለው ያምናሉ። ከዚህም ተነስተው ከዚህ በኋላ አራማጅነትን (Activism) መሠረት ያደረጉ እንቅስቃሴዎች እንጅ የፓርቲ ፖለቲካ ለውጥ ያመጣል ብለው እንደማያምኑ ይናገራሉ። “አሁን ያለው የፓርቲ ፖለቲካና የእስካሁኑ ትግል እርሾ ሁኖ ይቀጥል በሚለው ሐሳብ አልስማም” የሚሉት አቶ ግርማ ነገሮችን በአዲስ አተያይና አዲስ አካሄድ ማስጀመር መልካም መሆኑን ይገልጻሉ።

“ተስፋ ብንቆርጥማ እዚህ ምን እንሠራለን?”
በታኅሣሥ 2001 የብዙ ግለሰቦችን ጥያቄ ይፈታል የተባለለት በኦሮሞ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እና የኦሮሞ ሕዝብ ኮንግረስ ፓርቲዎች ሁለት መሆናቸውን ትተው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦ.ፌ.ኮ.) በሚል አዲስ ስያሜ ተዋህደው አንድ ወደ እንቅስቃሴ መግባታቸው ለብዙዎች ተስፋ የሰጠ እርምጃ ነበር። ኦ.ፌ.ኮ. ከዛን ጊዜ ወዲህ ከሌሎች አራት ፓርቲዎች ጋር በመሆን ‹መድረክ› የተባለ ግንባር በመፍጠር እየተንቀሳቀሰም ይገኛል።
ኦ.ፌ.ኮ. በሐገሪቱ ውስጥ ካሉት ዘጠኝ የፌደራል ክልሎች መካከል በሕዝብ ብዛትና በቆዳ ስፋት ደረጃ ትልቁ በሆነው የኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰው ብቸኛው ፓርቲ ነው ለማለት በሚያስችል መልኩ የሚገኝ ሲሆን፤ ፓርቲው የብዙዎችን ትኩረት የሚስበውም ከዚህ አቅሙ አንፃር ነው። ነገር ግን ባለፉት አምስት ወራት በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከተካሔዱት ሕዝባዊ ተቃውሞች ጋር በተያያዘ የድርጅቱ ዋነኛ አመራሮች የታሰሩበት ሲሆን በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ በቡሌ ሆራ ከተማ የቀረች አንድ የፓርቲ ቢሮ ብቻ እንዳለችው የድርጅቱ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በጥርጣሬ ይገልጻሉ። የድርጅቱ ሠላማዊ ታጋዮች ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. በክልሉ እየወሰደው ባለው ርምጃ ተጠቂዎች እንደሆኑ የገለጹት ዶ/ር መረራ የፓርቲያቸው ድል አድርገው የሚቆጥሩት “ሕዝቡን በተለያዩ መንገዶች አንቅተነው አሁን እኛ ባንኖርም መብቱን የሚያውቅና ለማስከበርም ቆርጦ የተነሳ ሕዝብ መፈጠሩ ነው” ይላሉ። ከዚህም ተነስተው “በፓርቲ ፖለቲካማ ተስፋ እንዴት እንቆርጣለን? ተስፋ የምንቆርጥ ከሆነማ እዚህ ምን እንሠራለን?” በማለት ተስፋ አስቆራጭ ነው ስለሚባለው የፖለቲካ ምኅዳር ላቀረብንላቸው ጥያቄ ምላሻቸውን ይሰጣሉ። “ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ከመቼውም ጊዜ በላይ የተዳከመው አሁን ነው” የሚሉት ዶ/ር መረራ “ኢሕአዴግ በ101 ችግሮች ተብትቦ ቢይዘንም አሁንም የሚሻለው ያሉብንን የመተባበር ችግሮች ተሻግረን ወደፊት መሄድ ነው” ይላሉ። መሪ የሚሆን ፓርቲ በሌለበት ሁኔታ ለውጥ እንኳን ቢመጣ በለውጥ ማግስት የሚፈጠረው ክፍተት የመረራ ስጋት ነው።

ፍሬውን ለማየት
በኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ እና የፖለቲካ ባሕል ውስጥ ተዘርዝረው የማያልቁ ችግሮች አሉ። ለችግሮቹ ተጠያቂ የሆኑ ዐብይ አካላት ቢኖሩም፣ ችግሮቹን ሁሉ ለአንድ ወገን ብቻ ጠቅልሎ መስጠት የትም እንደማያደርስ ከአጥኚዎች እስከ ፖለቲከኞች ድረስ ይስማማሉ።
አቶ ልደቱ አያሌው “ኢሕአዴግ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ዋነኛው ችግር ቢሆንም ብቸኛው አይደለም፤” ይላሉ። “ኢሕአዴግን የችግሩ አካል ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ፖለቲካ የመፍትሔ አካል አድርጎ ማየት ያስፈልጋል። እስከዛሬ ድረስ የሚጠቆሙት መፍትሔዎች በሙሉ በኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. መቃብር ላይ ለማድረግ የሚታሰቡ መሆናቸው ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. በተፃራሪው እንዲሠራ አድርጎታል” ይላሉ። ስለዚህ ወደ መድብለ ፓርቲ የሚደረገው ጉዞ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን የችግሩ ብቻ ሳይሆን የመፍትሔው አካል ማድረግ አለበት። በሁለተኝነት፣ አቶ ልደቱ በተመሳሳይ መንገድ “ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመፍትሔው አካል ነን፤ ነገር ግን የችግሮቹም አካል እንደሆንን ማመን አለብን። ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ውስጥ ያሉ ችግሮች በሙሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ውስጥም አሉ። ይህንን አምነን የተሻለ ሁነን ለመገኘት ራሳችንን የመገምገም እና ውስጣዊ ዴሞክራሲን ለመለማመድ መሥራት አለብን” ይላሉ።
ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በበኩላቸው፣ “ችግር ስላለ ነው እዚህ ያለነው” በማለት ነው ነገሩን የሚያብራሩት። “ፓርቲ መመሥረት አንችልም፤ ማኅበረሰባችን ለድርጅት ግንባታ ገና ነው፤ አምባገነንም ድርጅቶች አማራጭ ሆነው እንዲያድጉ አይፈልግም፤ ይሄ ወደትግል የመጣንበት ምክንያት ነው። ስለዚህ… ወደትግል የመጣንበት ምክንያት ውጤት ሆኖ ከትግል ሊያስወጣን አያስፈልግም።… ሁሉ ነገር የተደላደለ ከሆነማ ቀድሞውን መምጣት አያስፈልገንም ነበር።” በማለት ችግሩ ስላለ ነው የገባንበት፣ ከውድቀቶቻችን እየተማርን እንቀጥላለን እንጂ ልንቀርፈው በገባነው ችግር ተገፍተን አንወጣም በማለት የፖለቲካ ትግሉ እስኪያፈራ ድረስ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ እንዲቀጥል ይመክራሉ።
አንጋው ተገኝ በሠላሳዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለ ወጣት ነው። ፀጉሩን ያጎፍራል። ሲናገር በብዙ ነገሮች እየተደነቀ ነው። አንጋው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የሰሜን ጎንደር አብረሃ ጅራ ወረዳ ኃላፊ በመሆን እጅግ ፈታኝ ጊዜያትን አሳልፏል። የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ የሀገሪቱ ክፍሎች መንቀሳቀስ የሚያስከፍለው ዋጋ ከባድ መሆኑን ደጋግሞ ይናገራል። የፓርቲው አመራር ሁኖ በሠራበት ወቅት ፓርቲ ስብሰባ እንኳን ማድረግ እጅግ ከባድ መሆኑን ያስታውሳል። ፖሊስና የደኅንነት ኃይሎች አመራሮቹን እየተከታተሉ ሲያስጨንቋቸው ‹የፓርቲው ሥራ ከሚቆም በሚል አንገረብ ወንዝ ወርደን እየዋኘን እንሰበሰብ ነበር› ይላል። እየዋኘን ሰው ወደኛ በመጣ ቁጥር እየተበታተንን፤ ሰው ራቅ ሲልልን ደግሞ እዛው ውኃው ውስጥ ሰብሰብ ብለን እየተንሳፈፍን ነበር ስብሰባ የምናደርገው የሚለው አንጋው በፓርቲ እንቅስቃሴ ምክንያት ስድስት ጊዜ ከሥራ ተባሮ ስድስት ጊዜ መመለሱን ሲገልጽ አንዳንዴ በሕይወት መቆየቴም ለኔ ግርም ይለኛል እያለ ነው። ይባስ ብሎ በሠላማዊ ትግል ቆርቦ በዚህ ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ የነበረው አንጋው ተገኝ የሰውም ሆነ የሰነድ ማስረጃ ሳይቀርብበት አሁን ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር ግንኙነት አለህ በሚል ምክንያት በመጨረሻ ለእስር የተዳረገ ሲሆን፤ እስር ቤት ሁኖም የታገለለትና የደከመለት አንድነት ፓርቲ ሲፈርስና በእሱ አባባል ‹መፈንቅለ አመራር› ሲካሄድበት ተመልክቶ ያዝናል። ለዚህ ሁሉ መሆን አንጋው ተጠያቂ የሚያደርገው ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ.ን ነው። ‹ሕግ የማይገዛው መንግሥት› እያለ ሁሌም ይገረማል። ይህ የኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ ችግር የገዥው ፓርቲ ቅጥ ማጣት ነው ከሚሉት ወገን የሚቀርበው ሐሳብ ትክክለኛ ተምሳሌት ነው።
ከዚህ አሳዛኝ ኹነት መለስ ብለን አርብ ሚያዚያ 28፣ 2008 ከጠዋቱ 4፡30 እስከ 5፡30 ድረስ በአንድ ሰዓት ውስጥ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጆች ለጽሑፉ ግብዓት የሚሆን መረጃ ለማግኘት በማሰብ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ መሠረት እንዲሁ አለፍ አለፍ እያልን በአሁኑ ወቅት በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው ከሚገኙ ሰባ አምስት ፓርቲዎች መካከል የሃያ አምስት የተቃዋሚ ፓርቲዎች የስልክ አድራሻ ላይ ስልክ የደወልን ሲሆን፤ ከሃያ አምስቱ ሙከራዎች መካከል ሁለቱን ስልኮች ያነሱልን ሕፃናት ሲሆኑ፣ የሰባቱ ስልክ ቢጠራም አይነሳም፤ የዐሥራ አምስቱ ስልክ ደግሞ ከነአካቴው የማይሠራ ሲሆን፤ የአንዱ ብቻ ማለትም ‘የኦሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ሕብረት’ ስልክ ላይ የፓርቲውን አመራር ልናገኝ ችለናል። በተመሳሳይ ጊዜ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ያደረግነው ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪም ስልኩ ሊነሳ ባለመቻሉ ማብራሪያ ማግኝት አልቻልንም። እንግዲህ ‹የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ ሰሞን ግርግር ከመፍጠር ያለፈ ምንም አይፈይዱም የሚለው ሐሳብ እንዲሁ ያለውን ሁኔታ ቀረብ ብሎ ካለማየት የሚመጣ ነው› የሚሉ ተችዎችም ሁሌም የሚፈተኑበት ጉዳይም ይሄው ተቃዋሚ ፓርቲ ተብለው የተመዘገቡት ፓርቲዎች በሚገባቸው ቦታ አለመዋላቸው ነው። ፓርቲዎቹ የስልክ እንኳን አድራሻ የሌላቸው/ቢኖራቸው እንኳን የማይሠሩ ስልኮችን ይዘው ለኢትዮጵያ ሕዝብ የለውጥ መሠረት ይሆናሉ ብሎ ማሰቡንም ያከብደዋል። ይህ ደግሞ ተቃዋሚዎች የራሳቸው ሥራ ሳይሠሩ ገዥውን ፓርቲ ማውገዛቸው ተገቢ አይደለም የሚለው ሐሳብ ተምሳሌት ነው።

ይህ ጽሑፍ በሃገር ቤት ታትሞ በወጣው ውይይት መጽሄት ላይ የወጣ ነው:: በሃገር ቤት ያላችሁ መጽሄቱን ገዝታችሁ በማንበብ ጋዜጠኞቹን አበረታቷቸው::

Sunday, May 29, 2016

Africans in India living ‘in fear’ after killing: envoys

Part-DEL-Del8400784-1-1-0 (1)New Delhi (AFP) – African nationals in the Indian capital live in a “pervading climate of fear and insecurity”, a group of African ambassadors has said, after the brutal murder of a Congolese teacher sparked allegations of racism.
The Group of African Heads of Mission said they may recommend their governments not to send students to India until safety conditions improve, following a string of what they say are unpunished racial attacks.
In the latest case, Masunda Kitada Oliver, from the Democratic Republic of the Congo, was allegedly bludgeoned to death in New Delhi on Friday night by three Indian men after an argument over an auto-rickshaw.
“Given the pervading climate of fear and insecurity in Delhi, the African Heads of Mission are left with little option than to consider recommending to their governments not to send new students to India, unless and until their safety can be guaranteed,” Alem Tsehage Woldemariam, Eritrean ambassador and dean of the group said in a statement Tuesday.
“Several attacks and harassment of Africans in India have gone unnoticed without diligent prosecution and conviction of perpetrators,” he said.
In an embarrassment for New Delhi, the envoys said they would not participate in Africa Day celebrations being organised by the Indian Council for Cultural Relations on Thursday.
They said the African community was in mourning over Oliver’s death and asked for the event to be postponed.
Oliver had completed his postgraduate study in India and was teaching at a private institute in the capital.
Police have arrested two of the three men accused in the attack but deny the murder was racially motivated.
India’s foreign ministry condemned the killing but said not every attack on an African national should be regarded as racist.
“Thousands of African students continue to pursue their education in India without any issues,” a foreign ministry spokesman said in a statement.
Junior minister V.K. Singh will meet mission heads and students to assure them of their safety, the spokesman said, without specifying a date.
In 2013, a Nigerian national was killed by a mob in western Goa state, with local politicians later comparing Africans to “cancer”.
Meanwhile in January, an Indian mob beat a Tanzanian woman and her male friends in Bangalore and set their car ablaze before dragging them off a bus, in an apparent revenge attack for an earlier road accident.
Delhi’s former law minister was also accused in 2014 of harassing African women after he led a vigilante mob through an area of the capital, accusing the women of being prostitutes.

ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ምኑ ነው?

(በኤልሳቤጥ ግርማ ከኖርዌይ)
በዚህ በያዝነው ወር በየዓመቱ ስለግንቦት 20 በተለያየ መልኩ ይሰበካል፣ ይገለጻል። ለሀገራችን ኢትዮጵያ ታምራዊ ለውጥ እንዳስመሰገበ ሁሉ ወሩን ሙሉ ሲተረክ መስማት እንደ ሀገራዊ መዝሙር የተለመደ ሆኗል:: በተለይ የሥርዓቱ ባለቤቶችና ደጋፊዎች ምስኪኑን ሕብረትሰብ ሳይቀር በማስገደድ ቀኗን “ልዩ ቀን” “የድል ቀን” “የስኬት ቀን” በማለት ሰይመው በአስረሽ ምችው ሲከበር ማየት ድፍን 25 ዓመታትን አስቆጠረ።eprdf-tplf

ጀግናው የኢህአዲግ ሰራዊት ደርግ ኢሰፓ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬዲዮ ጣቢያ ተቆጣጥሮታል ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሦስት ብለው እንዳበሰሩን በእርግጥ ለጥቂቶች ግንቦት 20 የድል ቀን ነው:: ምክንያቱም ሀገሪቱን በአንባገነናዊ አገዛዝ ለማስተዳደርና የስልጣን ጥማታቸውን ለማርካት መሰረት የጣሉባት እና የአስራ ሰባት ዓመት የልፋት ዋጋቸውን ያገኙባት ልዩ ቀን ናትና:: በዚች ቀን ህብረተሰቡን በምስጢራዊ የአገዛዝ ስልት ለማስተዳደርና ስልጣናቸውን ዘላለማዊ ለማድረግ የነበራቸው ሕልም እውን የሆነባት ቀን ናትና በልዩ አከባበር ቢያከብሯት ሲያንሳት እንጂ አይበዛባትም::
የተወሰኑ የስራዓቱ አቀንቃኞችም ስለቀኗ መልካምነትና ከዚያች ቀን በኃላ አገራችን ኢትዮጵያ በልማት ጎዳና የገስገሰች፣ የዜጎች አኩልነት የተረጋገጠባት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት፣ ሰባዊ መብቶች የተከበሩባት፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ የታየባት፣ ህብረተሰቡን በእኩል የሚያስተዳድር መንግስትና ሕግ መንግስት የተመሰረተባት አገር እንድትሆን ግንቦት 20 ታሪካዊ የድል አሻራ እንደጣለች በኩራት አፋቸውን መልተው ይናገራሉ:: ይባስ ብለው ከውጭ ወራሪ ወይም ቅኝ ግዛት ኢትዮጵያን ነፃ ያወጧት ይመስል ግንቦት 20ን የነፃነት/ሀገራዊ ቀን ለማድርግ የሚሞክሩ ብልጣብልጥ የስራዓቱ ደንገጡሮችም አሉ::
በእርግጥ የደርግ አንባገነን መንግስት የአጼ ኃይለ ስላሴ መንግስትን ገርስሦ በምትኩ ወታደራዊ ጁንታ በመመስረት ስሙን በመቀያየር አገዛዙ ለ17 ዓመታት ኢትዮጵያን በብዙ ዘርፈ ብዙ ችግሮች በተለይ ሀገሪቱን መለወጥ ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡትን 60 ሚኒስተሮች በመረሸን፣ ነጭና ቀይ ሽብር በማለት ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማስጨፍጨፉ የኢትዮጵያ ህዝብ የደርግን ስርዓት አንቅሮ ተፍቶት ነበር። የለውጥ ያለሽ ብሎ በመጮህ ከደርግ አረመኔያዊ የጭካኔ አገዛዝ ነጻ ሊያወጣው የሚችል መለኮታዊ ኃይል እስኪፈልግ ድረስ የኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ ለውጥ ፈላጊ ሆነ።
ህወሓት የህዝቡን ብሶትና እሮሮ ተጠቅሞ 17 ዓመት ጫካ ውስጥ ያረገዘውን መርዝ ለመርጨት ግንቦት 20 ደርግን ገርስሦ በትረ ስልጣኑን ጨበጠ። እዚህ ላይ ወያኔ የደርግን ስርዓት ሳያይና በትንሹም ቢሆን ለውጥ እንዲመጣ ጥረት ሳያደርግ ለትግል ወደ ጫካ መግባቱ ሀገራዊ ለውጥ አሳስቦት ሳይሆን የብሄር ፖለቲካ ጥማት እንደሆነ በትክክል መገንዘብ ይቻላል፤እያየነውም ነው። የብሄር ፖለቲካ ደግሞ እንደ ኢትዮጵያ በርካታ ብሄር ብሄረሰቦችን ለምታስተናግድ ሀገር ቀርቶ ለየትኛውም የአለም ሀገራት የማይበጅ መሆኑ የታወቀ ነው። ኢትዮጵያም የከፋፍለህ ግዛውና የጎሳ ፖለቲካ እንደማይጠቅማት ከዘመነ መሣፍንት ትምህርት ቀስማ ነበር። ዳሩ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ የደርግን ሥርዓት ጥላቻና ሽሽት ዘረኛው ወያኔን ግንቦት 20 በሩን ከፍቶ እጁን ዘርግቶ ተቀበለ።
ወያኔዎች የደርግን ሥርዓት ገርስሰው መንግስቱ ኃይለ ማርያምን ወደ ዝምባብዌ ካስኮበለሉ በኋላ ሥልጣናቸውን ለማጽናት የይስሙላ ህገ መንግሥት አርቅቀው አጸደቁ። ለተወሰኑ ዓመታትም የነጻነት በርን ለመከፈትና ስላምና መረጋጋትን ለማስፈን የመጡ እስኪመስል ድረስ ሰላምን ሰበኩ። ከደርግ ጋር ንክኪ አላቸው ተብሎ የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን በሙሉ እስር ቤት ወረወሯቸው። ከገጠር እስከ ከተማ ህብረተሰቡ ለራሱ መጠበቂያ ብሎ የገዛዉን ትጥቅ ሳይቀር በሙሉ አስፈቱ። የኢትዮጵያ ህዝብ ግንቦት 20 በየዓመቱ “የድል ቀን” እያለ እንዲዘምር ተደረገ።
በእውኑ ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ምኑ ነው? ይህ ጥያቄ በተለያየ መልኩ በሁላችንም አይዕምሮ ውስጥ እንደሚመላለስ እርግጠኛ ነኝ። መልሳችን ግን በራሳችን ምዕናባዊ እይታ ስለምንመለከተው የተለያየ ሊሆን ይችላል፤ ሆኖም ግን ከሁለት አማራጮች ሊዘል አይችልም። ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔዎች እንደሚሉት “የድል ቀን” ወይም ብዙዎች እንደሚስማሙበት “የውድቀት ቀን” መሆን አለበት። ወያኔዎችና ደጋፊዎቻቸው ግንቦት 20ን “የድል ቀን” ማለታቸው በእርግጥም ትክክል ናቸው። ምክንያቱም በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የአንባገነን ስልጣናቸውን ያፀኑበት እና በሦስቱም ዘርፍ ማለትም ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩበት ቀን ነውና።
እውነታው ሲገለጥ ግን ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የውድቀት እና የውርደት ቀን እንጂ በምንም መመዘኛ የድል ቀን ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም ለአንድ ሀገር የድል ቀን ሲባል ዜጎቿ እኩል ተጠቃሚ ሊያደርግ የሚችል በጎ አጋጣሚ ወይም የኩራት ምንጪ ሲፈጠር ብቻ ነው። ግንቦት 20 ግን ከዚህ በተቃራኒው መሆኑን ግልጽ ሊያደርግ የሚችል ብዙ ማሳያዎች ከመኖሩም ባሻገር በኢትዮጵያና በህዝቦቿ ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ችግር ዘርዝሮ መናገር ይቻላል።
“የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
የኢትዮጵያ ህዝብ ከግንቦት 20 የተቀበላቸውን ገጸ እርግማኖች ለማሳያ ያክል እንደሚከተለው እናያለን፤
የብሄር ፖለቲካ የተፀነሰበት
የህወሓት ማፍያ ቡድን ገና ከጅምሩ ሃገራዊ ፍቅር ሰንቆ እንዳልመጣ ከስሙ መረዳት ይቻላል። የትግራይ ነጻ አውጪ ቡድን ብሎ መሰየሙ ለኢትዮጵያና ለህዝቧ እንዳልቆመ ለመረዳት ነብይነት አያሻውም ነበር። የከፋፍለህ ግዛው መርህን በማንፌስቶው ይፋ አድርጎ ይንቀሳቀስ እንደነበር ሰነዶች ህያው ማስረጃ ናቸው። ለስልጣን ማራዘሚያ በዋናነት የተጠቀመበት ዋናና ትልቁ አጀንዳ የብሄር ፖለቲካን ነው። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ካልሆነ በስተቀር ከስልጣን ሊወርድ የሚችልበት ምንም አይነት አጋጣሚ እንደሌለ በሚገባ ያውቃልና። የብሄር ፖለቲካ እያራመደ እርስበርሳችን እንዳንተማመን በብሄር ለያይቶናል። ይሄ የናንተ መሬት ነው፣ ይህ ደግሞ የነሱ ነው ወዘተ እያለ በቡድን ከፋፍሎናል። በብሄሮች መካከል መግባባት እንዳይኖር እነእገሌ እንዲህ አደረጓቹህ፣ ታሪካችሁ እንዲህ ነው በማለት መጀመርያ መምጣት ያለበት ብሄር ነው ወዘተ እያለ የብሄር ጥላቻ እንዲሰፍን ሀውልት ሰርቶልናል። አንድ ዜጋ ኢትዮጵያዊ ነኝ ከማለት ይልቅ በውሸት የብሄር እኩልነት ስም ኦሮሞ፣አማራ፣ ጉራጌ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ጋምቤላ እያለ በየቦታው እራሱን እያዋረደ እርስ በእርሳችን በጥላቻ እንድንናቆር ማድረጉ የወያኔ የብሄር ፖለቲካ ውጤት ነው። ስለዚህም ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የድል ቀን ሳይሆን የብሄር ፖለቲካ የተፀነሰበት የውርደት ቀን ነው። “የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
ትውልድ ገዳይ ሥርዓተ ትምህርት የተቀረጸበት
ትምህርት ቤቶች ለአንድ ሀገር ተተኪ ዜጋ ፈጣሪ ተቋም እንደመሆናቸው መጠን የሃገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ፣ ታሪክንና ባህልን ከማሳወቅ ባለፈም በማንነት ላይ የተመሰረተ ጥራት ያለው ዜጋ ለማፍራት የሚቀረጸው ሥራተ ትምህርት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። ነገር ግን ወያኔ የቀረጸው ሥርዓተ ትምህርት ግን ትውልድን ገዳይና የተማሪዎችን አይዕምሮ ለምርምርና ጥናት የማይጋብዝ ዘላቂና አስተማማኝ ያልሆነ ጥራት የጎደለው ሥርዓተ ትምህርት ነው። ትምህርት ቤቶችም ተማሪዎችን በጥሩ ሥነ ምግባርና ባህልን ከማሳዎቅ አንጻር አስተምሯቸው ዝቅተኛና ከዚህ ግባ የማይባል መሆኑ ለትውልዱ መጥፋት ሌላው የወያኔ የስርዓቱ ውጤት ነው። ትምህርት ቤቶችን ስንመለከት ከተቀረጸላቸው ሥርዓተ ት/ት ጀምሮ ትውልድን ለመቅረጽ ቀርቶ በዜግነት ደረጃም እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚናገር ትውልድ እንዲጠፋ በማድረግ ረገድ ግንቦት 20 የራሷን ጥቁር ጠባሳ ጥላለች። አንዳንድ የዘመነ ወያኔ ተማሪዎች የሀገረን ታሪክ በሚገባ ካለማዎቅ የተነሳ ቅኝ ግዛት በተገዛን ኑሮ ሲሉ መስማት የሥርዓተ ትምህርት ውድቀቱን ማሳያ አንዱ መንገድ ነው።
የሃገር ዳር ድንበር የተደፈረበት
አንድ ሀገር የድል ቀን የምታከብር ከሆነ ለሀገርና ለህዝብ የሚቆረቆር መንግሥት አላት ማለት ነው። መንግሥት ካለ ደግሞ የሃገር ሉዓላዊነት ተጠብቆ፣ ታሪኳ ሳይበረዝና ሳይፋለስ ለትውልድ መተላለፍ ይችላል ማለት ነው። ወያኔ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ግን የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ዳር ድንበሯ የተደፈረባት፣ ወደቧን ያጣችበትና ታሪኳ የተበረዘበት ዘመን ነው። ድሮ አባቶቻችን ቅኝ አንገዛም በማለት ታሪካችንና ባህላችን ሊበረዝ ከቶ አይችልም ብለው አጥንታቸውን ከስክሰው፣ ደማቸውን አፍስሰው፣ ውድ ህይወታቸውን ሰውተው ዳር ድንበሯን ከነሙሉ ክብሯ ያቆዩልንን ሀገር ወያኔ ለአረብና ህንድ ባለሃብቶች ማቀራመቱ ሳያንሰው ሱዳን የድርሻሽን ውሰጅ ብለው በመማጸን ላይ እንደሆኑ ስንሰማ በእውነትም ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የውርደትና የውድቀት ቀን ነው። ዜጎቿ በሄዱበት ሞትና እንግልቱ ሳያንሳቸው በእራሳቸው ሀገር በሌላ ዜጋ እንደ እንስሳ ደማቸው ሲፈስና ህጻናት በገፍ ተግዘው ሲሄዱ ከማየት በላይ ምን የተለየ ውርደትና ውድቀት ይኖራል። “የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
ህዝቦቿ ለሞት፣ለስርና በስደት ለውርደት የተዳረጉበት
በወያኔ አገዛዝ ከ1983 እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ከግንቦት ወር ጀምረን በግፍ ውድ ህይወታቸውን በስውርና በአደባባይ የተቀሰፉ፣ ለስር፣ ለእንግልትና ለስደት የተዳረጉ ዜጎችን የሰማይ አምላክ ይቁጠራቸው እንጂ በአኃዝ ማስቀመጥ እጅጉን ይዘገንናል። ተፈጥሯዊና ሰባዊ መብቶች በይፋ ተገርስሰዋል። የስርዓቱ አባል፣ ደጋፊና አገልጋይ ካልሆነ በስተቀር በሀገሩ ምድር ቀና ብሎ የመናገር፣ የመጻፍ፣ የመደራጀት እና የመስራት መብቶች ፈጽመው መገደባቸው የአደባባይ ምስጢር ነው። ወያኔዎች ግንቦት 20ን የድል ቀን ብለው ማክበር ከጀመሩ ጀምሮ በሀገሪቱ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የግፍ ጽዋ ሞልቶ ፈሷል። ህዝቦቿ በሄዱበት ሁሉ የውርደት ካባ እየተከናነቡ ተቆርቋሪ ያጣ ዜጋ በመሆኑ ዋይታና ልቅሶው ከመቸውም በላይ ጨምሯል። “የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
በአጠቃላይ ኢትዮጵያ አገራችን የተለያየ መልክና መገለጫ ያላቸው በርካታ መንግሥታትን ያስተናገደች አገር ብትሆንም ለዘመናት ታሪኳን፣ ባህሏን፣ እምነቷን፣ አንድነቷን፣ ድል አድራጊነትን እና ዳር ድንበሯን ጠብቃ አስጠብቃ የኖረች እና መተሳሰብን፣ መከባበርን፣ እንግዳ ተቀባይነትን፣ ዘርንና ጎሳን መሰረት ሳታደርግ ለዘመናት የቆየች የጀግኖች አገር ነበረች። ነገር ግን ግንቦት 20 የለገሰን የአሳርና የግፍ ፍሬዎች በቀላሉ የማይሽሩ እኩይ ተግባር ናቸውና ታሪካዊ አገራችንን አደጋ ላይ ጥሏታል። ስለሆም ጊዜ ሳንሰጥ “የድል ቀን” የሚለውን ተረት ተረት ወደ ጎን በመተው በአንድነትና በህብረት ዛሬውኑ የውርደትን ቀን ወደ የድልና የክብር ቀን ሊቀየር ይገባል። ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የድል ቀን ሳይሆን የሞት፣የውድቀትና የውርደት ቀን ተብሎ ይስተካከል!ምነው ሽዋ! ድንቄም የድል ቀን…………

wanted officials